Dr. Bogalech G Memorial G/Hospital, Durame

Dr. Bogalech G Memorial G/Hospital,  Durame This is our official page where you can find the latest updates on our service. We strive

10/09/2022

ለመላው ኢትዮጰያዊን እና ወድ የሆስፒታሉ ሠራተኞች እና ተገልጋዮች በሙሉ እንኳን ለ2015 አድስ ዓመት በሰላም በጤና አደረሰን /አደረሳችሁ !!!
አድሱ ዓመት የፍቅር ፣የሰላም ፣የደስታ ፣የስከት እና የብልፅግና ዓመት እንድሆንላችሁ መልካም ምኞቱን ይገልጻል ዶክተር ቦጋለች ገብሬ መታሰቢያ አጠቃላይ ሆስፒታል፡፡

01/09/2022

የዶ/ር ቦጋለች ገብሬ መታሰቢያ አጠቃላይ ሆስፒታል የማስፋፊያ ፕሮጀክት ሥራ የመሠረት ድንጋይ በደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ የተከበሩ ዶ/ር ባዩሽ ተስፋዬ እና በከምባታ ጠምባሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ መለሰ አጭሶ ተቀመጠ።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪ እና የደቡብ ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ባዩሽ ተስፋዬ በመርሀ ግብሩ ላይ ባደረጉት ንግግር መንግሥት ለጤናው ዘርፍ ፕሮጀክቶች ቅድሚያ እንደሚሰጥ ገልፀው ዛሬ የመሠረት ድንጋይ የተቀመጠለት የሆስፒታል ማስፋፊያ ፕሮጀክት እውን እንዲሆን በተሠራው ሥራ ልክ ጥራቱን የጠበቀ ግንባታ እንዱከናወን ተገቢው ክትትል ይደረጋል ብለዋል።

የከምባታ ጠምባሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ መለሰ አጭሶ ፕሮጀክት መጀመር ብቻ ሳይሆን ፍፃሜውን አግኝቶ ለህብረተሠቡ ተገቢውን አገልግሎት መስጠት እንዲችል በቅርብ ክትትልና ቁርጠኝነት እንደሚሠራ ገልፀው ማንኛውም የልማት ተግባር ሊሠራ የሚችለው ሀገር ሲኖር በመሆኑ አሸባሪው ሕወሓት ሀገር እንዳያፈርስ መላው ሕዝብ ከመንግሥት ጎን በመቆም ሁለንተናዊ ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።

የግንባታ ሥራውን የሚሠራው ኒሃርኒ ኮንስትራክሽን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት ግንባታውን በተቀመጠው የአንድ ዓመት ከስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ጨርሶ ለማስረከብ ቃል ገብቷል።

የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ወንድሙ ዳንኤል እንዳሉት የዞኑን አጠቃላይ የጤና ሽፋን ለማሳደግ በተሠራው ሥራ 87 በመቶ ማድረስ የተቻለ ሲሆን የኅብረተሰቡን የጤና አገልግሎት ተጠቃሚነትን በዘላቂነት ለማረጋገጥ በጥራትና ኢፍትሃዊነት ላይ ትኩረት ተሠጥቶ ሊሠራ እንደሚገባ አሳስበዋል።

በምረቃ መርሀ ግብሩ ላይ የከምባታ ጠምባሮ ዝፕን አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት፣ የከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ማናጅመንት አካላት፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሆስፒታሉ ማኅበረሰብ፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተሳታፊ መሆናቸው ታውቋል።

የዶ/ር ቦጋለች ገብሬ መታሰቢያ አጠቃላይ ሆስፒታል ከከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 'በጎነት ለጤናችን' የክረምት የበጎ ፈቃድ መርሀ ግብር በዞኑ አስተዳደር ቅጥር ...
23/08/2022

የዶ/ር ቦጋለች ገብሬ መታሰቢያ አጠቃላይ ሆስፒታል ከከምባታ ጠምባሮ ዞን ጤና መምሪያ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 'በጎነት ለጤናችን' የክረምት የበጎ ፈቃድ መርሀ ግብር በዞኑ አስተዳደር ቅጥር ግቢ ውስጥ በመካሔድ ላይ ነው።

በጎነት ለጤናችን በተሰኘው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሀ ግብር የስኳር፣ የደም ግፊት እና ሌሎች ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ምርመራ ለ1000 ሰዎች በነፃ የሚሰጥ መሆኑ ተገልጿል።

መርሀ ግብሩን የከምባታ ጠምባሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ መለሰ አጭሶ በይፋ አስጀምረውታል።

15/07/2022
16/06/2022
16/06/2022

በከምባታ ጠምባሮ ዞን ዶ/ር ቦጋለች ገብሬ መታሰቢያ አጠቃላይ ሆስፒታል ዱራሜ በእናቶችና ህፃናት ህክምና ማዕከል አንዲት እናት ሦስት ወንድ ልጆችን በሠላም ተገላገለች።

ሦስቱም ሕፃናት በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኙም ተገልጿል።

የሕፃናቱ እናት ወይዘሮ ትግስት ሎዳሞ እንደተናገረችው ከእርግዝና ወቅት ጀምሮ የሕክምና ማዕከሉ ባለሙያዎች ተገቢውን ክትትል ያደርጉላት የነበረ ሲሆን በወሊድ ወቅትም በተደረገላት በባለሙያዎች እገዛ ሦስት ልጆችን በሰላም በምጥ መገላገሏን ገልፃለች።

ለመውለድ ከገባችበት ሰዓት ጀምሮ የሕክምና ማዕከሉ ሐኪሞች እና አዋላጅ ነርሶች ተገቢውን የሕክምና አገልግሎት እንዳደረጉላት የገለፀችው ወ/ሮ ትግስት ሎዳሞ ለተደረገላት አገልግሎትም መላውን የተቋሙን ባለሙያዎች አመስግናለች።

የዛሬዎቹን ሦስት ወንድ ልጆች ጨምሮ የአራት ልጆች እናት የሆነችው ወይዘሮ ትግስት ሎዳሞ ከዚህ በፊት መንታ ወልዳ እንደማታውቅና አሁን ሦስት ልጆችን በሰላም መገላገሏ እንዳስደሰታት ተናግራለች።

የወይዘሮ ትግስት ሎዳሞ ባለቤት አቶ ብርሀኑ ጴጥሮስ በበኩላቸው ባለቤታቸው ከእርግዝና ወቅት ጀምሮ በተቋሙ ተገቢውን ክትትል ስታደርግ እንደነበር አውስተው በወሊድ ወቅትም የሆስፒታሉ ባለሙያዎች በተሻለ ሙያዊ ስነምግባር ለባለቤታቸው ተገቢውን የህክምና በመስጠታቸው ባለቤታቸው ያለምንም ችግር በሰላም ሦስት ልጆችን መገላገላቸውን ገልፀዋል።

እንደ አቶ ብርሀኑ ጴጥሮስ ገለፃ ባለቤታቸው በተቋሙ ያለምንም ክፍያ በነፃ ተገቢውን የወሊድ አገልግሎት ማግኘታቸውን በመግለፅ በወቅቱ በተቋሙ የእጅ ጓንት ባለመኖሩ ከውጭ መገዛታቸውን ግን ገልፀዋል።

በዶክተር ቦጋለች ገብሬ መታሰቢያ አጠቃላይ ሆስፒታል የእናቶችና ህፃናት ህክምና ማዕከል አስተባባሪ እና የፅንስና ማህፀን ስፔሻሊስት ዶክተር አብነት አዳነ ተቋሙ አንድም እናት በወሊድ ምክንያት መሞት የለባትም በሚል መርህ ለእናቶች ነፃ የወሊድ አገልግሎት እንደሚሰጥ ገልፀዋል።

ማዕከሉ ለበርካታ እናቶች ያለምንም ክፍያ ተገቢውን የወሊድ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ የገለፁት ዶ/ር አብነት አዳነ እንዲህ አይነት ከሁለት በላይ የሆኑ መንትዮች መወለዳቸው አልፎ አልፎ የሚፈጠር ነገር መሆኑንም አብራርተዋል።

ማዕከሉ በሚሰጠው አገልግሎት ከሁለት ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ በዞኑና አጎራባች ዞኖች የሚገኙ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እያደረገ ይገኛል ያሉት ዶ/ር አብነት አዳነ ተቋሙ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የግብዓት እጥረቶች እያጋጠሙት በመሆኑ ኅብረተሰቡና ባለድርሻ አካላት ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።

15/06/2022

በደቡብ ክልል መንግሥት የበጀት ድጋፍ 147 ሚሊዮን በላይ በሆነ ብር ለሚገነባው የዶ/ር ቦጋለች ገብሬ መታሰቢያ አጠቃላይ ሆስፒታል የማስፋፊያ ፕሮጀክት የቦታ ርክክብ ተደረገ።

በክልሉ መንግሥት 147 ሚሊዮን 95 ሺህ 621 ብር የተመደበለት የሆስፒታል ማስፋፊያ ፕሮጀክት ባለ ሁለት ወለል የእናቶችና ሕፃናት ጤና ሕክምና ሕንፃ፣ ባለ ሦስት ወለል የሐኪሞች ማደሪያ ሕንፃ፣ የተኝቶ ሕክምና ሕንፃ፣ የተመላላሽ ሕክምና ሕንፃ፣ የምርመራ ማዕከል ሕንፃን ጨምሮ የእግረኞች መንገድ እና ሌሎች ሥራዎች የተካተቱበት ስለመሆኑ በርክክቡ ወቅት ተገልጿል።

ጨረታውን ያሸነገው ነሀርኒ ኮንስትራክሽን ሥራዎቹን በሁለት ዓመት ውስጥ ለማጠቃለል ውል እንደፈፀመ ነው የክልሉ ጤና ቢሮ ተወካይ የገለፁት።

በቦታ ርክክቡ ወቅት የደቡብ ክልል ጤና ቢሮ እና የደቡብ ክልል ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ተወካዮችን ጨምሮ የከምባታ ጠምባሮ ዞን ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የሆስፒታሉ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት እና ማናጅመንት አካላት ተሳታፊ ሆነዋል።

17/04/2022
23/12/2021

Address

Durame

Telephone

+251465540921

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dr. Bogalech G Memorial G/Hospital, Durame posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram

Category