11/12/2025
የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ
____________
የጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በ Medicine, Nursing, Public Health, Anesthesia, Pharmacy, Medical Laboratory Science, Midwifery, Dental Medicine, Medical Radiology Technology, Environmental Health, Psychiatric Nursing, Pediatric & Child Health Nursing, Emergency & Critical Care Nursing, Surgical Nursing, Physiotherapy, Optometry እና Human Nutrition ሙያዎች በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቀው የብቃት ምዘና ፈተና ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ ለሚገኙ የጤና ባለሙያዎች በታህሳስ 2018 ዓ.ም የብቃት ምዘና ፈተና ለመስጠት በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡
ስለሆነም አዲስም ሆነ ነባር፣ የመንግስትም ሆነ የግል ተቋማት ተመዛኞች በኦንላይን http://hpe.moh.gov.et/hple ላይ በመግባት እንድትመዘገቡ እና የኦንላይን ምዝገባው ከታህሳስ 02/2018 እስከ ታህሳስ 12/2018 ዓ.ም ብቻ የሚቆይና ከተጠቀሰው ቀን በኋላ ምንም ዓይነት የምዝገባ ጥያቄ የማናስተናግድ መሆኑን አውቃችሁ በተጠቀሱት ቀናት እንድትመዘገቡና ሲስተሙ የሚሰጣችሁን የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No) የያዘ ስሊፕ print አድርጋችሁ በመያዝ ስትመዘገቡ በመረጣችሁት የፈተና ጣቢያ በፈተናው ወቅት እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡
ማሳሰቢያ፦
ተመዛኞች ምዝገባውን ለማካሄድ የኢትዮጵያ ዲጅታል መታወቂያ- ፋይዳ (Ethiopian Digital ID Card) ግዴታ መሆኑን አውቃችሁ የፋይዳ መለያ ልዩ ቁጥር (FIN) በትክክል እንድታስገቡ እያሳሰብን ይህ ሳይሆን ቀርቶ ለሚፈጠረው መጉላላት የጤና ሚኒስቴር ሃላፊነት የማይወስድ መሆኑ እናሳውቃለን።
ለተጨማሪ መረጃ የጤና ሚኒስቴር ቴልግራም ቻናል ይመልከቱ t.me/M0H_EThiopia
Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB