Gambella woreda government communication affair

Gambella woreda government communication affair Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Gambella woreda government communication affair, AIDS Resource Center, Gambella, Gambela.

በጋምቤላ ክልል አልፎ አልፎ የሚከሰቱ የፀጥታ ችግሮችን በዘላቂነት ለመቅረፍ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች ተሳትፎ ሊጠናከር እንደሚገባ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ አስገነዘቡ።ርዕ...
02/04/2024

በጋምቤላ ክልል አልፎ አልፎ የሚከሰቱ የፀጥታ ችግሮችን በዘላቂነት ለመቅረፍ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች ተሳትፎ ሊጠናከር እንደሚገባ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ አስገነዘቡ።

ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ እና ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ቴንኩዌይ ጆክ በክልሉ ከሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አካሂደዋል።

ከጋምቤላ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት (መጋቢት 24/ 2016 ዓ.ም)

ርዕሰ መስተዳደሩ አቶ ኡሞድ ኡጁሉ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት በክልሉ አልፎ አልፎ የሚከሰተውን የጸጥታ ችግር በዘላቂነት ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የተፎካካሪ ፓርቲዎች ተሳትፎ ሊጠናከር ይገባል ብለዋል።

ሰሞኑን የተከሰተን የጸጥታ ችግር በመፍታት ሰላሙን ወደ ቀድሞ ለመመለስ በሚደረግ ጥረት በክልሉ የሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ጨምሮ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ እንደሚገባ አስታውቀዋል።

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ቴንኩዌይ ጆክ በበኩላቸው ሰላም በሌለበት የፖለቲካም ሆነ የልማት ስራዎችን ለማከናወን እንደማይቻል ገልጸዋል።

ስለሆነም ለክልሉ ዘላቂ ሰላምና ልማት መረጋገጥ ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች በትብብር ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በክልሉ ሰፍኖ የቆየውን ሰላም ለማደፍረስ የሚጥሩትን ለማጋለጥና ድርጊታቸውን ለማክሸፍ መንግስት ከሚያደርገው ጥረት በተጓዳኝ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሚና ሊጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል።

አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሰጡት አስተያየት ለተፈጠረው የጸጥታ ችግር የጋራ መፍትሄ ለመሻት ከክልሉ መንግስት ጋር በቅንጅት ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

አልፎ አልፎ የሚከሰተውን የጸጥታ ችግር በጋራ በመፍታት የክልሉን ሰላም ዘላቂ ማድረግ እንደሚገባ አስረድተዋል።

ተቻችሎና ተከባብሮ የመኖር የቀደመ ታሪካቸውን በማጠናከር የክልሉን ሰላም ለማስቀጠል ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ መንቀሳቀስ እንደሚኖርባቸው አመላክተዋል።

በውይይቱ ላይ ብልጽግናን ጨምሮ በክልሉ የሚንቀሳቀሱ አራት የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ተሳትፈዋል።

በጋምቤላ ክልል ያለውን ሰላም ዘላቂ ለማድረግ እንዲቻል ከ5ቱ ቀበሌና ሴክተር መስሪያ ቤቶች የተወጣጡ ሴቶች ጋር ዉይይት ተካሂዷል።ውይይቱን የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ባንቻየሁ...
02/04/2024

በጋምቤላ ክልል ያለውን ሰላም ዘላቂ ለማድረግ እንዲቻል ከ5ቱ ቀበሌና ሴክተር መስሪያ ቤቶች የተወጣጡ ሴቶች ጋር ዉይይት ተካሂዷል።

ውይይቱን የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ባንቻየሁ ድንገታ፣ የክልሉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ክርምስ ሌሮና ምክትል ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ አለሚቱ አለባቸው መርተውታል።

በጋምቤላ ክልል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የልማት ጣቢያ ሰራተኞች ሚና ሊጠናከር እንደሚገባ የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ...
01/04/2024

በጋምቤላ ክልል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የልማት ጣቢያ ሰራተኞች ሚና ሊጠናከር እንደሚገባ የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው በRLLP እና በFSRP ፕሮጀክቶች ድጋፍ በጋምቤላ ወረዳ፣ በመንገሺና በጎደሬ ወረዳዎች ለሚገኙ የልማት ጣቢያ ሰራተኞች ለአራት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የመጀመሪያ ዙር የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት ጀምሯል።

ከጋምቤላ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት (መጋቢት 23/2016 ዓ.ም)

ስልጠናው እየተሰጠ የሚገኘው በጋምቤላና በሜጢ ከተማ ሲሆን በሰብል ልማት፣ በእንሰሳት እና አሳ ሀብት፣ በተፋሰስ ልማትና ችግኝ ጣቢያ አዘገጃጀት እንዲሁም በሰርቶ ማሳያ አተገባበር ላይ ያተኮረ ስልጠና እንደሆነ ተገልጿል።

የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡጁሉ ሉዋል በስልጠናው መክፈቻ ላይ እንዳሉት በክልሉ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት የልማት ጣቢያ ሰራተኞች ሚና ሊጠናከር ይገባል ብለዋል።

የስልጠናው ዋና አላማ በአጠቃላይ በክልል ደረጃ በግብርናው ዘርፍ ያለውን ከፍተት ለመሙላት ፣ የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ይቻል ዘንድ በቀጥታ ከአርሶና ከፊል አርብቶ አደሩ ጋር በመገናኘት የሙያ ድጋፍ የሚያደርጉ የልማት ጣቢያ ሰራተኞችን የመፈፀም አቅም ለማጎልበት ያለመ እንደሆነ ገልፀዋል።

በተለይም በየግብርና ልማት ጣቢያ ሰራተኞችና በሌሎች የግብርና ልማት ባለድርሻ አካላት መካከል ጠንካራ ግንኙነት በመፍጠር የግብርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችል ስልጠና እንደሆነ አብራርተዋል።

የማጃንግ ብሔረሰብ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ዮናስ ተኮምሳ በበኩላቸው ስልጠናው የልማት ጣቢያ ሰራተኞችን የአቅም ክፍተት የሚሞላ እንደሆነ ጠቁመዋል።

በመሆኑም ሰልጣኞች ለተከታታይ አራት ቀናት በሚሰጠው የአቅም ግንባታ ስልጠና በንቃት በመሳተፍ የአርሶ አደሩን ህይወት ለመለወጥ እንዲተጉ ጥሪ አቅርበዋል።

ስልጠናው ለተከታታይ አራት ቀናት የሚሰጥ ሲሆን ከሶስቱ ወረዳዎች የተውጣጡ 202 የልማት ጣቢያ ባለሙያዎች እንደሚሰለጠኑ ከወጣው መርሀ ግብር ለማወቅ ተችሏል።
@የጎደሬ ወ/የመ/ኮሙ/ጉ/ጽ/ቤት

በክልሉ ዘላቂ ሰላምና ልማት እንዲረጋገጥ የመንግስት ሰራተኞች የበኩላቸዉን አስተዋፅኦ ሊያበረክቱ እንደሚገባ ተገለፀ።የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ፣ ገቢዎች ቢሮ፣ ፕላንና ልማት ቢሮ እንዲሁም ግዢና ን...
01/04/2024

በክልሉ ዘላቂ ሰላምና ልማት እንዲረጋገጥ የመንግስት ሰራተኞች የበኩላቸዉን አስተዋፅኦ ሊያበረክቱ እንደሚገባ ተገለፀ።

የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ፣ ገቢዎች ቢሮ፣ ፕላንና ልማት ቢሮ እንዲሁም ግዢና ንብረት አስተዳደር ሰራተኞችና አመራሮች በክልሉ ወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ ውይይት አካሂደዋል።

ከ በክልሉ ዘላቂ ሰላምና ልማት እንዲረጋገጥ የመንግስት ሰራተኞች የበኩላቸዉን አስተዋፅኦ ሊያበረክቱ እንደሚገባ ተገለፀ።

የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ፣ ገቢዎች ቢሮ፣ ፕላንና ልማት ቢሮ እንዲሁም ግዢና ንብረት አስተዳደር ሰራተኞችና አመራሮች በክልሉ ወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ ውይይት አካሂደዋል።

ከአኙዋሃ ብሔረሰብ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት (መጋቢት 23/2016 ዓ.ም)

የመንግስት ሰራተኞቹ በሰጡት አስተያየት ሰላም የሁሉም ነገር መሰረት በመሆኑ ለክልሉ ዘላቂ ሰላም መስፈን በጋራ እንሰራለን ብለዋል።

የሰላም ችግር በክልሉ የተጀመረውን የልማት ሥራ የሚያደናቅፍ ከመሆኑም በላይ በክልሉ በአንድነት የሚኖረውን ህዝብ ኑሮ የሚያናጋ መሆኑን ተናግረዋል።

መንግስት የህግ የበላይነትና ሰላምን ለማረጋገጥ ለጀመራቸው ስራዎች መቃናት የበኩላቸውን ድርሻ ለማበርከት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

በመሆኑም ችግሩን ለመፍታትና የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ቀጣይነት እንዲኖራቸው እያንዳንዱ ሰራተኛ በጋራ ለሰላሙ ዘብ መቆም እንደሚገባ ገልፀዋል።

የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡቦንግ ኡቶው በዚሁ ጊዜ እንዳሉት የክልሉ መንግስት የተፈጠረውን የሰላም ችግር ለመፍታት ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

በክልሉ ያለውን ሰላም ይበልጥ ለማጎልበት ህዝቡ አንድነቱን ሊያጠናክር እንደሚገባ የጠቆሙት አቶ ኡቦንግ በየደረጃው የሚገኙ ሰራተኞችም የበኩላቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።

የውይይቱ ዓላማ በከተማው አልፎ አልፎ የሚፈጠረውን የፀጥታ ችግር በመፍታት ቀደም ሲል ወደ ነበረው ሰላምና ፍቅር በመመለስ ሰራተኛው የዕለት ተዕለት ስራውን እንዲያከናውን ማስቻል ነው ብለዋል።

የመንግስት ሰራተኞቹ በሰጡት አስተያየት ሰላም የሁሉም ነገር መሰረት በመሆኑ ለክልሉ ዘላቂ ሰላም መስፈን በጋራ እንሰራለን ብለዋል።

የሰላም ችግር በክልሉ የተጀመረውን የልማት ሥራ የሚያደናቅፍ ከመሆኑም በላይ በክልሉ በአንድነት የሚኖረውን ህዝብ ኑሮ የሚያናጋ መሆኑን ተናግረዋል።

መንግስት የህግ የበላይነትና ሰላምን ለማረጋገጥ ለጀመራቸው ስራዎች መቃናት የበኩላቸውን ድርሻ ለማበርከት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

በመሆኑም ችግሩን ለመፍታትና የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ቀጣይነት እንዲኖራቸው እያንዳንዱ ሰራተኛ በጋራ ለሰላሙ ዘብ መቆም እንደሚገባ ገልፀዋል።

የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡቦንግ ኡቶው በዚሁ ጊዜ እንዳሉት የክልሉ መንግስት የተፈጠረውን የሰላም ችግር ለመፍታት ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

በክልሉ ያለውን ሰላም ይበልጥ ለማጎልበት ህዝቡ አንድነቱን ሊያጠናክር እንደሚገባ የጠቆሙት አቶ ኡቦንግ በየደረጃው የሚገኙ ሰራተኞችም የበኩላቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።

የውይይቱ ዓላማ በከተማው አልፎ አልፎ የሚፈጠረውን የፀጥታ ችግር በመፍታት ቀደም ሲል ወደ ነበረው ሰላምና ፍቅር በመመለስ ሰራተኛው የዕለት ተዕለት ስራውን እንዲያከናውን ማስቻል ነው ብለዋል።

በጋምቤላ ክልል ወንድማማችነትና እህትማማችነትን በማጠንከር የክልሉን ዘላቂ ሰላም ማስቀጠል እንደሚገባ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ ገለፁ።''ወንድማማችነትና እህትማማችነት ይቅደም...
31/03/2024

በጋምቤላ ክልል ወንድማማችነትና እህትማማችነትን በማጠንከር የክልሉን ዘላቂ ሰላም ማስቀጠል እንደሚገባ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ ገለፁ።

''ወንድማማችነትና እህትማማችነት ይቅደም'' በሚል መሪ ቃል የጋምቤላ ክልልና የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች የፅዳት ዘመቻ አካሂደዋል።

ከጋምቤላ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት (መጋቢት 22/ 2016 ዓ.ም)

የዘመቻው ዋና አላማ አካባቢን ፅዱ ከማድረግ ጎን ለጎን የወንድማማችነትና እህትማማችነትን መንፈስ ለማጎልበት እንዲረዳ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት በምንቀሳቀስባቸው የስራ ዘርፎች የአብሮነትና በጋራ የመልማት አስተሳሰብን ማስቀደም ከሁሉም አካል የሚጠበቅ መሆኑን ገልፀዋል።

በክልሉ አልፎ አልፎ እየተከሰተ ያለውን ግጭት ለማስቀረት የሚያስችል በርካታ ስራ እየተሰራ መሆኑን ያብራሩት ርዕሰ መስተዳድሩ ፅንፈኝነትንና ጥላቻን ማስወገድ ይገባል ብለዋል።

ሰላም የሰው ልጆች የሕልውና መሰረት በመሆኑ ሰላምን ለማምጣት የሚያስችሉ መፍትሔዎች ላይ ማተኮር እንደሚገባ ርዕሰ መስተዳድሩ አስገንዝበዋል።

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ቴንኩዌይ ጆክ በበኩላቸው የነበረውን የፀጥታ መደፍረስ ለማስተካከል እንዲቻል የወንድማማችነትና እህትማማችነት ስሜት ማጎልበት አለብን ብለዋል።

አንድነታችንን በመጠበቅ ለክልሉ ዘላቂ ሰላም መላው ሕዝብ ተባባሪ መሆን መቻል እንዳለበትም አስገንዝበዋል።

የዜጎችን የአንድነትና የአብሮነት እሴት በማጠናከር ወንድማማችነትና እህትማማችነትን የሚያጸና ቀጣይነት ያለው ስራ ማከናወን እንደሚገባም አብራርተዋል።

ከተሞች ፅዱ እንዲሆኑ አመራሩ ሚናው የጎላ መሆኑን የጠቀሱት ደግሞ በብልፅግና ፓርቲ የጋምቤላ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አሽኔ አስቲን ናቸው።

ከሁሉም ነገር በላይ ከተዋደድንና በጋራ አብሮ መስራት ከቻልን የትኛውንም ፈተና ማለፍ እንችላለን ብለዋል።

30/03/2024
በጋምቤላ ክልል የሚገኙ የስደተኛ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ወደ መንግስት የማስተላለፍ ሂደት ዙሪያ የምክክር እና የግንዛቤ ማስጨበጥ መድረክ ተካሄደ።መጋቢት 19/2016 ዓ.ም (የጋምቤላ ክል...
30/03/2024

በጋምቤላ ክልል የሚገኙ የስደተኛ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ወደ መንግስት የማስተላለፍ ሂደት ዙሪያ የምክክር እና የግንዛቤ ማስጨበጥ መድረክ ተካሄደ።

መጋቢት 19/2016 ዓ.ም (የጋምቤላ ክልል ትምህርት ቢሮ)

የክልል ትምህርት ቢሮ የትምህርት ተቋማት ማስፋፋት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ የሆኑት አቶ ኳንግ አኳይ የምክክር መድረኩ ተሳታፊ እንግዶችን የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ የፕሮግራሙን ዓላማ አጠር ያለ ማብራሪያ በመስጠት የምክክር መድረኩን ከፍተዋል።

የትምህርት ሚኒስቴር የስደተኞች ትምህርት ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ ጌታቸው አድማሱ በምክክር መድረኩ የስደተኛ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ወደ መንግስት ተዘዋወሩ ማለት የሌሎች ድጋፍ ሰጭ ድርጅቶች ሙሉ በሙሉ ድጋፋቸውን ያቋርጣሉ ማለት ሳይሆን ከትምህርት ሚ/ር ጀምሮ ሌሎች መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የተለመደ ድጋፍ የሚቀጥል መሆኑን አጽንኦት ሰጥተው አብራርተዋል።

አቶ ጌታቸው ትኩረት ሰጥተው ካነሷቸው አበይት ጉዳዮች ለምንድን ነው ትምህርት ለስደተኞች ማድረስ የተፈለገው? የስደተኛ ትምህርትን የማስማማት እና የመዋሃድ አላማን እውን ለማድረግ ከባለድርሻ አካላት ምን ይጠበቃል? የሚለው ሲሆን ሀገራችን ኢትዮጵያ የአጠቃላይ የስደተኞች ምላሽ ማዕቀፍ ፓይለት ሀገር መሆኗ፣ በስደተኞች ላይ ያላት ዓለም አቀፍ እምቅ ተቀባይነት፣ ኢትዮጵያ በስደተኞች ዙሪያ የጅቡቲን ስምምነት ተግባራዊ የማድረግ ቁርጠኛ መሆኗ እና መሠል ጉዳዮችን ሰፊ ጊዜ ወስደው አብራርተዋል።

አቶ ጌታቸው አያይዘው እንደገለጹት በGEQIP-E የተሰሩ ስራዎችን እና ለስደተኞች እንዲሁም ለአካባቢው ማህበረሰብ የትምህርት ስራውን ምቹ ለማድረግ የተደረጉ ሙያዊ እና ቁሳዊ ድጋፎችን አንስተዋል።

የጋምቤላ ክልል ትምህርት ቢሮ የGEQIP-E/የአጠቃላይ ትምህርት ማረጋገጫ ፕሮግራም ለፍትሀዊነት አስተባባሪ የሆኑት ዶክተር በለጠ ዳምጤ በትግበራ ወቅት እና በቀጣይ ሂደት ሊያጋጥሙ የሚችሉ ተግዳሮቶችንና ተስፋዎችን ጠቅሰው እስከ አሁን የተከናወኑ ተግባራትን በፎቶ ማስረጃ በማስደገፍ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

የክልል ትምህርት ቢሮ መረጃ እና ዕቅድ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ለይኩን ጌታነህ የስደተኛ እና የአካባቢ ማህበረሰብ የአንደኛና መካከለኛ ደረጃ ተማሪዎች መጽሐፍ ህትመት ሂደትና ወደ መንግስት የተሸጋገሩ ትምህርት ቤቶች የመምህራን እና የአስተዳደር ሠራተኞች ቅጥር እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው በቅርቡ የመማር ማስተማር ስራው እንደሚጀምር አሳውቀዋል።

በውይይት መድረኩ የክልል ፋይናንስ ባለሙያዎች፣ የክልል ትምህርት ቢሮ የስራ ኃላፊዎች፣ ከስደተኛ ጋር የሚሰሩ ባለድርሻ አካላት፣ የአኝዋ ብሄረሰብ ዞን ም/አስተዳዳሪ፣ የአኝዋ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ፣ አራቱ ስደተኛ የሚያስተናግዱ ወረዳ ም/አስተዳደሮች፣ የወረዳ ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊዎች፣ የወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ባለሙያዎች፣ የቀበሌ ሊቀመንበሮች፣ የስደተኛ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሳነ መምህራን ተገኝተዋል።

በውይይቱ መዝጊያ ላይ የተገኙት የጋምቤላ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ላክዴር ላክባክ ስኬታማ ስራ ለመስራት እና የስደተኛ ትምህርት ቤቶች ወደ መንግስት የማሸጋገር ሂደት ውጤታማነት የሁሉንም ርብርብ የሚጠይቅ መሆኑን አውስተው ለተሳታፊዎች ለጥያቄና አስተያየት እንዲሰጡ ዕድል ሰጥተዋል።

በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ ከአቅራቢዎች ተሰጥቶ የማጠቃለያ ሀሳብ ከመድረክ ቀርቦ የምክክር መድረኩ በስኬት ተጠናቋል።

በጋምቤላ ክልል ሰላምን በዘላቂነት ለማስቀጠል የኃይማኖት አባቶች ማህበረሰባዊ እሴትን በማጎልበት ረገድ የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ እንደሚገባ ጥሪ ቀረበ፡፡የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁ...
30/03/2024

በጋምቤላ ክልል ሰላምን በዘላቂነት ለማስቀጠል የኃይማኖት አባቶች ማህበረሰባዊ እሴትን በማጎልበት ረገድ የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ እንደሚገባ ጥሪ ቀረበ፡፡

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉን ጨምሮ ሌሎች አመራሮች በጋምቤላ ከተማ ከሀይማኖት አባቶች ጋር በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ ውይይት አካሂደዋል።

ከጋምቤላ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት (መጋቢት 21/2016 ዓ.ም)

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ በውይይቱ ወቅት እንዳሉት በክልሉ አልፎ አልፎ የሚከሰቱ ግጭቶችን በማስወገድ ሰላምን በዘላቂነት ለማስቀጠል የኃይማኖት አባቶች ሚና ሊጠናከር ይገባል ብለዋል።

ከዚህ ቀደም ግጭቶች ሲከሰቱ ሰላምን ለማምጣት ይጠቀሙበት የነበረውን ማህበረሰባዊ እሴት በማጎልበት ለክልሉ ሰላም ጉልህ ሚና ሊጫወቱ እንደሚገባ አስረድተዋል።

የሀይማኖት አባቶች በማህበረሰቡ ዘንድ ያላቸውን ተቀባይነት በመጠቀም መልካም እሴት የማነፅ ልምድ ተጠቅመው ክልሉን ካለበት አስቸጋሪ ወቅት ሊታደጉት በሚያስፈልግበት ጊዜ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

በመሆኑም የኃይማኖት አባቶች በክልሉ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ከፍተኛ ድርሻ ሊወጡ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ቴንኩዌይ ጆክ በበኩላቸው የሰላም ሰባኪ የሆኑት የኃይማኖት አባቶች በክልሉ ዘላቂ ሰላም ለማምጣት ግንባር ቀደም ሆነው ሊሰሩ እንደሚገባ አመልክተዋል።

አለመግባባቶችን በሰላማዊ መንገድ መፍታት አስፈላጊ መሆኑን ያመለከቱት አቶ ቴንኩዌይ፤ በክልሉ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን መንግስት እያደረገ ያለውን ጥረት በመደገፍ የሀይማኖት አባቶች የድርሻቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።

በብልጽግና ፓርቲ የጋምቤላ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሽኔ አስቲን በዚሁ ጊዜ እንዳሉት ሰላምና ሀይማኖት የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች በመሆናቸው ለሰላም መስፈን መስራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።

ሰላም ለክልሉ ሁለንተናዊ እድገት ወሳኝ በመሆኑ ሰላም ለማስፈን ሁሉም ሃይማኖት ተቋማት እምነቱ በሚፈቅደው አስተምሮ መሰረት ስለ ሰላም አስፈላጊነት የእምነቱ ተከታዮችን ማስተማር እንደሚኖርባቸው አስታውቀዋል።

የውይይቱ ተሳታፊ የኃይማኖት አባቶች በሠጡት አስተያየት ትላንት የነበረውን አንድነት በማማጣት በጎሳና በብሄር መከፋፈል በመተው ለክልሉ ሰላም በጋራ መቆም እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች እየታዩ ያሉትን ግጭቶች ለማስቆምና የክልሉ ሰላም ወደ ቀድሞው ይመለስ ዘንድ ከመንግስት ጎን በመቆም እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡

በተለይም ወጣቶች ወደ ግጭት እንዳይገቡና በስነምግባር የታነፁ ሆነው እንዲያድጉ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ማህበረሰባዊ እሴቶችን በማጎልበት ማስተማርና መምከር ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡

30/03/2024
ዛሬ የምዕራብ ኦሞ ዞን በመጎብኘቴ ደስታ ተሰምቶኛል።  የተፈጥሮ ውበት እና እምቅ ሀብት ሞልቶ የፈሰሰበት፤ በትክክለኛ የልማት ድጋፍ እና የሰላም ከባቢ ሁኔታ ለኢትዮጵያ ሀገራችን የእድገት ር...
30/03/2024

ዛሬ የምዕራብ ኦሞ ዞን በመጎብኘቴ ደስታ ተሰምቶኛል። የተፈጥሮ ውበት እና እምቅ ሀብት ሞልቶ የፈሰሰበት፤ በትክክለኛ የልማት ድጋፍ እና የሰላም ከባቢ ሁኔታ ለኢትዮጵያ ሀገራችን የእድገት ርምጃ በእጅጉ አስተዋፅዖ የሚያደርግ አካባቢ ነው። ምንም እንኳ ሁሉንም የልማት ፍላጎት ማሟላት ጊዜ የሚወስድ ቢሆንም ኢትዮጵያ ሁሉን አቀፍ ለሆነ የልማት መፍትሔ መሠረት ለመጣል በፅናት መቆሟን ለአካባቢው ሕዝብ አረጋግጫለሁ።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

የወሊሶ አጠቃላይ ሆስፒታል ከአንድ የ28 አመት ወጣት ሆድ ዉስጥ  ሚስማር: መርፌ: ሽቦና የጥርስ መፋቂያን ጨምሮ 15 ባዕዳን ነገሮችን በቀዶ ህክምና ማዉጣቱን ገለጸ።ኦቢኤን መጋቢት 21/20...
30/03/2024

የወሊሶ አጠቃላይ ሆስፒታል ከአንድ የ28 አመት ወጣት ሆድ ዉስጥ ሚስማር: መርፌ: ሽቦና የጥርስ መፋቂያን ጨምሮ 15 ባዕዳን ነገሮችን በቀዶ ህክምና ማዉጣቱን ገለጸ።

ኦቢኤን መጋቢት 21/2016- የወሊሶ አጠቃላይ ሆስፒታል ከአንድ የ28 አመት ወጣት ሆድ ዉስጥ ሚስማር: መርፌ: ሽቦና የጥርስ መፋቂያን ጨምሮ 15 ባዕዳን ነገሮችን በቀዶ ህክምና ማዉጣቱን ገለጸ።

የቀዶ ህክምናዉ ቡድን መሪ ዶ/ር ኤሊያስ ሰኝ ለኦቢኤን እንደተናገሩት ከታካሚዉ የሆድ ክፍል 3 ሚስማሮች: 2 ቀጫጭን ሽቦዎች: አንድ መርፌ: 9 የእንጨት ጥርስ መፋቂያዎችና ሌሎች ባዕዳን ነገሮች አንድ ሰአት በፈጀ ቀዶ ህክምና መዉጣት መቻሉን አስታዉቀዋል።

ታካሚዉ በአዕምሮ ህመም ምክንያት የህክምና ክትትል ሲያደርግና መድሃኒት ሲጠቀም እንደነበረ የሆስፒታሉ ስፔሻሊስት ሃኪም ዶ/ር ኤሊያስ ሰኝ አብራርተዋል።

ነዋሪነቱን በደቡብ ምዕራብ ሸዋ አመያ ወረዳ ያደረገዉ ይህ ታካሚ ከአንድ በፊት በአዕምሮ ህመም ምክንያት ሲከታተል የነበረዉን ህክምናና መድሃኒት አቋርጧል።

ታካሚዉ ክትትሉን ከማቋረጡም በላይ አሁን በቀዶ ህክምና ከሆዱ የወጣዉ ባዕድ ነገር ይኖራል ብሎ ያሰበም ሆነ ተገቢዉን ምርመራ ያደረ አካል አለመኖሩን ነዉ የገለጹት።

ዶ/ር ኤሊያስ ሰኝ እንደተናገሩት መሠል ክስተቶች ሊፈጠሩ ስለሚችሉ ማህበረሰቡ የአእምሮ ህመም ያለባቸዉን ግለሰቦች ከተለመደዉ ክትትል በዘለለ በጤና ተቋማትና በሰለጠነ ባለሙያ ድጋፍ ሊያደርጉላቸዉ እንደሚገባ መክረዋል። ዘገባዉ የኮቲ ተፈራ ነዉ።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ዩትዩብ፦Youtube.com/OBNoromiyaa?sub_confirmation=1
ፌስቡክ OBN አፋን ኦሮሞ ፡ http://facebook.com/OBNAfaanoromo
ፌስቡክ OBN አማርኛ፡ http://facebook.com/OBNAmharic
ፌስቡክ OBN ሆርን ኦፍ አፍርካ: https://www.facebook.com/OBNHornofAfrica
ፌስቡክ OBN እንግልሽ : http://facebook.com/OBNEnglish.
ትክቶክ ፡ : https://www.tiktok.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/OBN_VoiceOfthepeople
ትዊተር፦ https://twitter.com/OBNoromiyaa
OBN Radio https://zeno.fm/radio/obnradio/
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን

የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ  አባልና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ ጽ/ቤት የፖለቲካና  አቅም ግንባታ ዘርፍ  ኃላፊ  በመሆን ሲያገለግሉ የነበሩ  አቶ ተዘ...
30/03/2024

የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ በመሆን ሲያገለግሉ የነበሩ አቶ ተዘራ ወ/ማሪያም ባጋጠማቸው ድንገተኛ ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዱ ቆይቶ ዛሬ መጋቢት 20/7/2016 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።

በአቶ ተዘራ ወ/ማሪያም ህልፈተ ህይወት የተሰማንን ጥልቅ ሃዘን እየገለፅን ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው፣ ለባልደረቦቻቸው መጽናናትን እንመኛለን።

Address

Gambella
Gambela

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gambella woreda government communication affair posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share