ሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ/Hadiya Zone Health Department

ሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ/Hadiya Zone Health Department This is the official page of Hadiya Zone Health Department. ይህ የሃድያ ዞን ጤና መም

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ የክልል ጤና ቢሮ የድጋፍ ቡድን በወረዳዎች ድጋፍ አድርጎ አጠቃላይ ግብረ መልስ ተሰጠ።‎            *******13/1/2018*********...
23/09/2025

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ የክልል ጤና ቢሮ የድጋፍ ቡድን በወረዳዎች ድጋፍ አድርጎ አጠቃላይ ግብረ መልስ ተሰጠ።
‎ *******13/1/2018*********
‎ቡድኑን የመሩት የክልሉ ጤና ቢሮ ምትክል ኃላፊ አቶ ሀብቴ ገ/ሚካኤል በዞኑ ውስጥ በሌሞ ሶሮና ምዕ/ሶሮ ወረዳ ላይ እስከ ጤና ኬላ ድጋፋዊ ክትትል መደረጉን አውስተው ዛሬ በምቀርበው ግብረ መልስ መነሻ ተጨማሪ ተቋማትን ማየት ያስፈልጋል ብለዋል።

‎በመቀጠልም የክልሉ ጤና ቢሮ እናቶችና ህፃናት ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ሌጅሶ ከጤና ኬላ እስከ ጤና ጽ/ቤት ድረስ የታዩትን ደካማና ጠንካራ ጎኖችን በሥፋት ለመምሪያ ማናጅመንት አቅርበዋል።

‎በቀረበው ግብረ መልስ መነሻ ከቤቱ ሰፊ ሀሳብ ተነስቶ በቀጣይ ክትትል በሚደረግበት ሂደት ላይ በመግባባት ለይ ተደርሷል።

‎በመጨረሻም የመምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ደሣለኝ ሹጉጤ ድጋፉ በዓመቱ ጅማሮ ላይ እንደመሆናችን ለቀጣይ ሥራችን ጠቃሚ ነው ብለው በጥንካሬ የተለዩትን ለማስፋትና በድክመት የተለዩትን ደግሞ ለማረም መሰል ድጋፎች እንደምደረግ አንስተው የዕለቱ ስብሰባ ተጠናቋል።

በ07/01/2018 ዓ/ም የሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ ዘርፈ ብዙ ኤች አይቪ ኤድስ መከ/መቆ/ዳይሬክቶሬት የ2017 ዓ/ም ዕቅድ አፈፃፀም   ግምገማ እና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ምክክር መድረ...
20/09/2025

በ07/01/2018 ዓ/ም የሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ ዘርፈ ብዙ ኤች አይቪ ኤድስ መከ/መቆ/ዳይሬክቶሬት የ2017 ዓ/ም ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ምክክር መድረክ ከሁሉም ወረዳዎች፣ ከተማ አስተዳደሮች፣ከጤና ጣቢያዎችና ሆስፒታሎች ከዞኑ ማናጅመንቶች ጋር አካሄዷል።
አጠቃላይ የዞኑ አፈፃፀም ሪፖርትና ዕቅድ ቀርቦ ውይይት ተደርጓል።

በቀረበው ሪፖርት እና ዕቅድ ላይ ሰፊ ሀሳቦች ተነስቶ ቀጣይ በዞኑ የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ ትኩረት በመስጠት መሰራት እንዳለበት በመግባባት የዕለቱ ስብሰባ ተጠናቋል።
በመጨረሻ ላይ የዞኑ የዘርፈ ብዙ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ከሁሉም ወረዳ እና ከከተማ ከዘርፉ አስተባባሪዎች ጋር የ2018 በጀት አመት ዕቅድ ላይ ተፈራርሞ ተጠናቋል።
ምንጭ:- ዘርፈ ብዙ ኤች አይቪ ኤድስ መከ/መቆ/ዳይሬክቶሬት

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀዲያ ዞን በዱና ወረዳ የክረምት በጎ ፈቃድ ወጣቶች አገልግሎት  ከተለያዩ ማህበራዊ መሠረቶች ጋር በመተባበር ለ200 ድጋፍ ለሚሹ ተማሪዎች  የደብተርና  የእስክብ...
18/09/2025

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀዲያ ዞን በዱና ወረዳ የክረምት በጎ ፈቃድ ወጣቶች አገልግሎት ከተለያዩ ማህበራዊ መሠረቶች ጋር በመተባበር ለ200 ድጋፍ ለሚሹ ተማሪዎች የደብተርና የእስክብርቶ ድጋፍና 37 unit ደም አሰባሰብ ማደረጉ ተገለፀ።

ለድጋፉ 87,000 ብር ከተለያዩ ማህበራዊ መሠረቶች መሰብሰቡ ተገልጿል።

***************************************
አንሾ፦መስከረም 08/2018 ዓ/ም የዱና ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት!

በወረዳው ሥር ከሚገኙ ከሁሉም መዋቅሮች የደሃ ደሃ ተማሪዎች በመለየት የተደረገው ድጋፍ የሰብኣዊነት ኃላፊነት ከመወጣት ባሻገር ለሌሎች አካባቢዎችም እንደ መልካም አርአያነት የሚሆን ተግባር ነዉ ተብሏል።

በድጋፉ መርሀግብር ላይ የተገኙት የዱና ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ በረከት ታገሠ እንደገለጹት ትምህርት የሁሉም እድገት ቁልፍ መሣሪያ በመሆኑ በትምህርት ላይ ተጨባጭ ለዉጥ ለማምጣትና ዘመኑን የዋጃ ዉጤት ለማስመዝገብ እንዲሁም የትምህርት ስብራትን ለመጠገን ያለዉን ቁርጠኝነት የሚያሣይ ቅንጅታዊ ሥራ ነዉ ብለዋል።

አቶ በረከት ጨምረዉም ትምህርት ለሀገር እድገትና ግንባታ ሀሳብ የሚያፈልቀዉን ትውልድ የሚንገነበበት ቁልፍ መሣሪያ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በአዳጊ ትዉልድ ላይ ዛሬ የተደረገው መልካም ተግባር ለቀጣይ ትዉልድ የኢትዮጵያዊያንን መደጋገፍ የሚለዉን መሪ የበለጠዉን እንደሚያጠናክር አሰይታቸዋል በማለት ተናግረዋል።

የዱና ወረዳ ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተሾመ ኤርታቦ በበኩላቸዉ በመልካም ልብ ማቀድና በቁርጠኝነት መሥራት ከተቻለ በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ ተወዳዳሪ መሆን የሚችሉ ዜጎችን ማፍራት ይቻላልም ያሉት የጽ/ቤቱ ኃላፊ ለዚህም በትምህርት ለይ መንግስት፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችና ህብረተሰቡ ተቀናጅቶና ተናቦ መሥራት ጊዜ ልሰጠው የሚገባ ጉዳይ አይደለም ብለዋል።

አቶ ተሾመ ኤርታቦ አክለዉም ተማሪዎች በወቅቱ በትምህርት ገበታቸው ላይ እንዲገኙ ለማስቻልና በትምህርት ብቁ የሆነ ዜጋ በመፍጠር የኢትዮጵያን ብልጽግና እዉን ለማድረግ ደጋግ የሆኑ ኢትዮጵያዊያን የተለመደዉንና የወትሮውን የመደጋገፍ ባህል ልያጠናክሩ ይገባል ብለዋል።

አንዳንድ የደብተርና የእስክብርቶ ድጋፍ የተደረገላቸዉ ተማሪዎችም ድጋፉ የሚያበረታታ እንዲሁም በትምህርታቸዉም ጠንከር ብሎ ተምረዉ ዉጤታማ በመሆን ሀገሩንና እራሳቸዉን ለማገልገል በቁርጠኝነት እንደሚማሩ በአስተያየታቸዉ ተናግሯል።

ተማሪዎቹም በተደረገላቸው ትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ እጅግ በመደሰት ድጋፍ ላዳራጉ አካላትም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በድጋፍ መርሀግብር ላይ የዱና ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ በረከት ታገሠ፣ የዱና ወረዳ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ታገሠ አበራ፣ የዱና ወረዳ አስተባባሪ አካላት፣ የዱና ወረዳ ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳዮች ጽ/ቤት ሠራተኞች እና ሌሎች ተገኝተዋል።

ዘገባዉ የዱና ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ነዉ።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ ሶሮ ወረዳ ና ከሥሩ የጁከራ ጤና ጣቢያ እንድሁም ምዕ/ሶሮ ወረዳና በሥሩ የጃቾ ጤና ጣቢያ ድጋፋዊ ክትትል ተካሄደ።‎                   ...
17/09/2025

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ ሶሮ ወረዳ ና ከሥሩ የጁከራ ጤና ጣቢያ እንድሁም ምዕ/ሶሮ ወረዳና በሥሩ የጃቾ ጤና ጣቢያ ድጋፋዊ ክትትል ተካሄደ።
‎ ******7/1/2018*******
‎በድጋፋዊ ክትትል የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የህክምና አገልግሎቶች ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሀብቴ ገ/ምካኤል፣የእናቶችና ህፃናት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ሌጅሶ እንድሁም የሀብት አሰባሰብ ኬዝ ቡድን አስተባባሪ አቶ ፀጋዬ ታዲዎስ ክልል ጤና ቢሮ የተሳተፉ ሆኖ ከዞን ጤና መምሪያም የመምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ደሣለኝ ሹጉጤን ጨምሮ ሌሎች ባለሙያዎችም ተሳታፊ ሆነዋል።

‎ድጋፋዊ ክትትሉ የ2018 ዓ.ም ተግባራት እንዴት እየተመሩ እንደሆነና ለቀጣይስ መሻሻል ያለባቸውን ጉዳዮች እንዴት ማሻሻል እንዳለበት አቅጣጫ የምሰጥ እንደሆነ አቶ ሀብቴ ገልፀዉ የምሰጡ ሀሳቦችን ለቀጣይ በትኩረት የምወሰዱ እንደሆነ አጽንዖት ሰጥተዋል።

‎ በየመድረኮችም በተለይ የወባን ጫና ለመከላከልና ለማከም ያለው ዝግጅትና አጠቃላይ ሂደት፣የቲብ በሽታን በአግባቡ ለይቶ ማከም በምቻልበት ሂደት፣የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ተግባራትን ለማሳለጥ ከወዲሁ መፈጸም በሚገባቸው ነጥቦች፣የእናቶች ማቆያ ተግባራዊ በምሆንበት ሁኔታ፣የባለሙያው duty አከፋፈል ላይ ባሉ ችግሮች እና ሌሎች የየጤና ጣቢያዎቹ ቦርድ አባላት መፍታት በሚገባቸው ነጥቦች በሰፊው የጋራ መግባባት ላይ መድረስ ተችሏል።

‎በመጨረሻም በጽ/ቤት እና በጤና ጣቢያ ደረጃ በተነሡ ነጥቦች መነሻ ከየወረዳ አስተባባሪ (ዋና አስተዳዳሪዎችን ጨምሮ) የጋራ መግባባት ላይ መድረስ ተችሏል።
ሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ!!

በመዕከላዊ ኢትዮጵያ ሀዲያ ዞን በሾኔ ከተማ አስተዳደር  የሾኔ ሆስፒታል የአዋቂ ICU እና ከወረቀት ንክኪ ነፃ አገልግሎት በይፋ ተመረቀ።         *******6/1/2018*********...
16/09/2025

በመዕከላዊ ኢትዮጵያ ሀዲያ ዞን በሾኔ ከተማ አስተዳደር የሾኔ ሆስፒታል የአዋቂ ICU እና ከወረቀት ንክኪ ነፃ አገልግሎት በይፋ ተመረቀ።
*******6/1/2018**********

የሾኔ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ወረቀት አልባ የማስጀመሪያ አገልግሎት እና adult ICU አገልግሎት መርሃ-ግብር የሀዲያ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ተሾመ አናሞ፣ የሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ ሀላፊ ተወካይ አቶ ምሻሞ ወርቅነህ፣ የሽኔ ከተማ ከንቲባ አቶ አበራ በዶሬና ሌሎች የምመለከታቸው አካላት በተገኙበት በይፋ ተመርቋል።

የሀዲያ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ተሾመ አናሞ በመድረኩ ተገኝተው ባሰሙት ንግግር ከተሞችን የብልጽግና ማዕከል ለማደረግ ማዘመን ማስጀመር ፣የአገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋ እና ከእጅ እና ወረቀት ንክኪ ነፃ የሆነ አሰራር መዘርጋት፣ ለሆስፒታሉ መልካም ጅምርና ለእድገቱ ወሳኝ ምዕራፍ ነው ብለዋል።

ደረጃ ማዘመን ከዚህ ቀደም የነበሩ ችግሮችን የሚፈታ፣ የሀብት ብክነትን የሚቀንስ፣ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን የሚቀርፍ፣ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል፣እርካታን ከፍ የሚያደርግ በማለት የማዘመን ስራው በይፋ መጀመሩን አብስረዋል።

ሆስፒታሉ በዚህ ልክ የጀመራቸው የማዘመን ተግባር የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፣ የውስጥ ገቢ ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ ጠቁመዋል ።

አቶ አበራ በዶሬ የሾኔ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መድረኩን በከፈቱበት ወቅት እንደገለጹት ፣ ሆስፒታሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሳየ የለው መሻሻል ሆስፒታሉን ከፍ ለማድረግ እየተደረገ ያለውን ጉዞ የሚደግፍ ነው ብለዋል።

የሾኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ አቶ አብርሃም ሎምቤ ይህንን አገልግሎት ለመጀመር ብዙ ዋጋ እንደከፈሉ ገልፀው ፣ ድጋፍ ያደርጉ አካላትን ሁሉ አመስግነዋል።

የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር አሸናፊ ኤርሚያስ የስራ አፈጻጸምን የተመለከተ አጭር ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን፣ በቀረበው ሪፖርት ላይ አጠር ያለ ውይይት ተደርጎ ሀሳብ ተሰጥቶበታል።

በዕለቱም የማዘመን ተግባር እና የሲስተም ስራዎችን፣ በሆስፒታል የጽኑ ህሙማን ICU ክፍል፣ በኮምፒዩተር ውስጥ የተሰሩ የቴክኖሎጂ ሽግግር ምን ይመስላል? የሚለው ምልከታ የተደረገ ሲሆን፤ የሰርቨር አገልግሎት እና አጠቃቀም ባለሙያዎች የተሰሩ ተግባራትንና የአግልግሎት አጠቃቀም ሂደትን በሚመለከት ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በሌላ ዜና የክረምት በጎ ተግባራት ማጠናቀቂያ ፕሮግራም በዱና ወረዳ ጤና ጽ/ቤት በተዘጋጀው የደም አሰባሰብ መረሃ ግብር 37 unit ደም ማሠባሠብ የተቻለ ሆኖ ሌሎች የክረምት በጎ ተግባራትም በቅንጅት ተከናውኗል።

ምንጭ

# ሾኔ ኮሙኒኬሽን
እና
#ዱና ወረዳ ጤና ጽ/ቤት

ዛሬ በተደረገ የደም ልገሳ ዘመቻ በሀገር-አቀፍ ደረጃ በአንድ ቀን የነበረውን ሪከርድ የሰበረ ከፍተኛው ዩኒት ደም ተሰበሰበ!!ነሐሴ 27/2017 ዓ.ምበዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ ...
02/09/2025

ዛሬ በተደረገ የደም ልገሳ ዘመቻ በሀገር-አቀፍ ደረጃ በአንድ ቀን የነበረውን ሪከርድ የሰበረ ከፍተኛው ዩኒት ደም ተሰበሰበ!!

ነሐሴ 27/2017 ዓ.ም

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ደም በመለገስ ህይወት እናድን በሚል መሪ-ቃል የደም ልገሳ ዘመቻ በዛሬው እለት የተካሔደ ሲሆን በሀገር-አቀፍ ደረጃ እስካሁን ድረስ በአንድ ቀን ውስጥ ተሰብስቦ ከነበረው ዩኒት ደም በቁጥር የሚበልጥ ተሰብስቧል።

የሆስፒታሉ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ይድነቃቸው ደዳቸው እንደተናገሩት ዛሬ በሆስፒታሉ የሚገኙ ሰራተኞች እና ተማሪዎች በተነሳሽነት ደም መለገሳቸውን አድንቀው ደም መለገስ ውዱ ስጦታ ነው ሲሉም አንስተዋል።

የሆስፒታሉ ማኔጂንግ ዳይሬክተርና የክረምት በጎ ስራዎች አስተባባሪ የሆኑት አቶ ተክሌ እጃጆ እንደገለጱት፦ ዛሬ በሆስፒታላችን የተደረገውን የደም መለገስ ዘመቻ ሌሎችም እንደ ምሳሌ በመውሰድ ሊደግሙት ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።

በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል የሆሳዕና ዲስትሪክት የደም ባንክ ዋና አስተባባሪ የሆኑት አቶ ጌታቸው ባሶሬ በንግግራቸው፦ ዛሬ በን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል በተደረገው የደም ልገሳ ዘመቻ 203 ዩኒት ደም በ አንድ ቀን ውስጥ መሰብሰቡ በሀገር-አቀፍ ደረጃ እስካሁን በአንድ ቀን ውስጥ ከተሰበሰበ ዩኒት ደም ከፍተኛው መሆኑን ጠቅሰው ከተባበርን የማናሳካው ነገር አይኖርም ሲሉ ተናግረዋል።

በመጨረሻም በበጎ ፍቃደኝነት ደም ለለገሱ የህክምና ተማሪዎችና የሆስፒታሉ ሰራተኞች እጣ በማውጣት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

ነሐሴ 27/2017 ዓ.ም
ምንጭ:-ዘገባው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/እ/ ሆስፒታል ህዝብ ግንኙነት ነው!!!
Let Your light shine in the Society!!

በን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል አቅም ላነሳቸው ወላጆች ድጋፍ ተደረገ!!ነሐሴ 27/2017 ዓ.ምበዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አቅም ላነ...
02/09/2025

በን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል አቅም ላነሳቸው ወላጆች ድጋፍ ተደረገ!!
ነሐሴ 27/2017 ዓ.ም

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አቅም ላነሳቸው ወላጆች ድጋፍ ተደርጓል።
በድጋፉም ከ 150 ለሚበልጡ ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁሶች እና ለ 30 እናቶች የእህል እና ዘይት ድጋፍ ተደርጓል።

በእለቱም የተገኙት የሆስፒታሉ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ይድነቃቸው ደዳቸው እንደተናገሩት፦ የበጎ-ፍቃድ ስራዎች እንደሀገርም እንደአከባቢም ባህል እየሆነ መምጣቱን በማንሳት ሁሉም ባለድርሻ አካላት ይህን መልካም ተግባር አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

የንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቺፍ እስተዳደርና ልማት ዳይሬክተር በተጨማሪም የክረምት በጎ ስራዎች ዋና አስተባባሪ የሆኑት አቶ ተክሌ እጃጆ በንግግራቸው፦
በ 2017 ዓ.ም የክረምት በጎ ስራዎች በስፋት መሰራታቸውን ጠቅሰው ዛሬም ከክረምት በጎ ስራዎች መካከል አንዱ የሆነው የማዕድ ማጋራት መርሀግብር መካሔዱን አንስተዋል።
አክለውም ዳይሬክተሩ በዚህ በጎ ስራ የተሳተፉ የሆስፒታሉ ባለሞያዎች ላሳዩት ትልቅ የሆነ ሰብአዊ ተግባር ከፍ ያለ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ ሀላፊ የሆኑት ዶ/ር ደሳለኝ ሽጉጤ እንደተናገሩት፦ ተማሪዎች መሰረታዊ የመማሪያ ቁሳቁሶችን በማጣት ከትምህርት ገበታቸው ሊቀሩ እንደማይገባ ጠቅሰው ዛሬ የምናስተምራቸው ተማሪዎች ነገ የሀገር ተረካቢ እንደሚሆኑም ጠቅሰዋል።
በመጨረሻም በዞኑ ማህበረሰብ ስም ለንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ያላቸውን ከፍ ያለ ምስጋና አቅርበዋል።

በመጨረሻም ድጋፍ የተደረገላቸው እናቶች በተደረገላቸው ድጋፍ እንደተደሰቱ በመናገር ለሆስፒታሉ ከፍ ያለ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ነሐሴ 27/2017 ዓ.ም
ምንጭ:-ዘገባው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/እ/ ሆስፒታል ህዝብ ግንኙነት ነው!!!
Let Your light shine in the Society!!

በሀዲያ ዞን የክረምት በጎ ተግባራትን በተመለከተ የኬሮል ሆስፒታል ለ100 ተማሪዎች የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።                  *******24/12/2017*******...
30/08/2025

በሀዲያ ዞን የክረምት በጎ ተግባራትን በተመለከተ የኬሮል ሆስፒታል ለ100 ተማሪዎች የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።

*******24/12/2017*******

የክረምት በጎ ተግባራት ላይ በሰፊው እየተሳቸፈ የሚገኘው ኬሮል ሆስፒታል በዛሬው ዕለት የኢኮኖሚ አቅማቸው አነስተኛ ከሆነ ቤተሰቦች ለተገኙ 100 ተማሪዎች የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል።

የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ ዶክተር ሎምባሞ ሊረንሶ በዚህ ወቅት እንዳሉት ሆስፒታሉ ከተመሠረተ 8 ወራትን ያስቆጠረ ሲሆን ለህብረተሰቡ በጤናው ዘርፍ አገልግሎት ከመስጠት በተጨማሪ በተለያዩ በጎ አድራጎት ተግባራት ላይ በመሳተፍ ለሀገር እና ለህዝብ አለኝታነቱን እያሳየ ይገኛል።

ዶክተር ሎምባሞ አክለውም ሆስፒታሉ በዛሬው እለት ካደረገው የደብተርና እስኪብርቶ ድጋፍ በተጨማሪ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን ተከትሎ በከተማ ፅዳት፣ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ወቅት የችግኝ ተከላ በማካሄድ እንዲሁም በሆሳዕና ማረሚያ ተቋም በመገኘት ለታራሚዎች ነፃ የህክምና አገልግሎት በመስጠት በጎ ስራ ላይ በመሳተፍ ላይ እንደሚገኝና በቀጣይም በሌሎች ተግባራት ላይ በንቃት የመሳተፍ እቅድ እንዳለው ተናግረዋል።

የሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ ሀላፊ የሆኑት ዶክተር ደሳለኝ ሽጉጤ በበኩላቸው፤ እንደ ዞን የጤናው ሴክተር ከሰኔ 5 እስከ ጳጉሜ 5 ድረስ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ በመሳተፍ ላይ እንደሚገኝ ገልፀው በዚህም በርካታ ተግባራት መከናወኑን ተናግረዋል።

ዶክተር ደሳለኝ አክለውም ሆስፒታሉ ላደረገው ድጋፍ ምስጋናቸውን በማቅረብ ሌሎች የጤና ተቋማት የህብረተሰቡን ጤና ከማስጠበቅ ባሻገር በበጎ ስራዎች ላይ መሳተፍ አለባቸው ሲሉ አሳስበዋል።

ሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ

በሀዲያ ዞን እየተተገበረ ያለው የክረምት በጎ ተግባራት ተጠናክሮ መቀጠላቸው ተገለፀ።‎                      ******17/12/2017******‎ከሰኔ አንድ ጀምሮ እየተሰራ የመጠ...
23/08/2025

በሀዲያ ዞን እየተተገበረ ያለው የክረምት በጎ ተግባራት ተጠናክሮ መቀጠላቸው ተገለፀ።
‎ ******17/12/2017******
‎ከሰኔ አንድ ጀምሮ እየተሰራ የመጠው የክረምት በጎ ተግባራት እስከ ነሐሴ መጨረሻ ድረስ የምቀጥሉ እንደሆነ የዞን ጤና መምሪያ ሃለፊ ዶ/ር ደሣለኝ ጠቁመው በእስከአሁኑ ተግባር በተለይም የጤና ምርመራዎች የችግኝ ተከላ ተላላፊ በሽታዎችን የመከላከል ተግባራትና ሌሎችም በሥፋት መሠራታቸውን ጠቁመው አሁንም የበለጠ መጠናከር እንዳለበት አንስተው በተለይም የደም አሰባሰብና የመህፃን ጫፍ ካንሰር ምርመራ የተሻለ አፈጻጸም ለማስመዝገብ ጥረት እንደምያስፈልግ ጠቁመዋሉ።

‎ በተያያዘም ተግባሩ በመምሪያ ደረጃ በተገመገመ ወቅት ከደም ማሰባሠብ ጋር zero ያስመዘገቡ ወረዳዎች ምዕ/ሶሮ, ጊምቢቹ, ሶሮ,ዱና, ጃጁራ,ጎምቦራ, ጊቤ, ሆማቾ, ሻሾጎ, ሲራሮ ሲሆኑ ሌሎችም በዝቅተኛ የሚፈረጁ መዋቅሮችም እንዳሉ ማለትም ፎንቆ,አንሌሞ,ምዕ/ባደዋቾ እና ምሻ እንደሆኑ ተመልክቷል።

‎በዛሬው ዕለትም በቦኖሻ ከተማ የበጎ ደም ማሰባሰብና ሌሎች የጤና ተግባራት የተሰሩ ሆኖ ይሀው ተግባር ዘየበለጠ ሊጠናከር እንደምገባም ተጠቁሟል።

በሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ WHO Epi week -32 የአደጋ ጊዜ ማስተባባሪያ ማዕከል  (PHEOC) በመምሪያ ደረጃ ተገመገመ፡፡‎          ********13/12/2017******‎‎የሀዲ...
21/08/2025

በሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ WHO Epi week -32 የአደጋ ጊዜ ማስተባባሪያ ማዕከል (PHEOC) በመምሪያ ደረጃ ተገመገመ፡፡
‎ ********13/12/2017******

‎የሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ ህብረተስብ ጤና አደጋ ማስተባበሪያ ማዕከል (PHEOC) የተለያዩ የጤና አደጋዎችን በመገምገም ግብረ መልስ በመስጠት የሚከሰቱ ጤና አደጋዎችን በፍጥነት ምለሽ በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ ማስተባበሪያ ማዕከሉ (PHEOC) በየሳምንቱ የድንገተኛ አደጋዎች የቅድመ ዝግጅት ፣ ማስጠንቀቂያና ምለሽ ስራዎችን እየገመገመ ይገኛል፡፡
‎ከሪፖርት ሙሉዕነት እና ወቅታዊነት አንፃር ፡- በሳምንቱ የሪፖርት ሙሉዓዊነት እና ወቅታዊነት አንፃር 100% ሲሆን ይህም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት፡፡
‎የወባ በሽታ በሚመለከት ፡- በሳምንቱ እንደ ዞን 1592 ታማሚዎች እና 0 ሞት ሪፖርት የተደረገ መሆኑና ከባለፈዉ ሳምንት አንፃር ሲታይ በ 99 (7%) ጨምሯል፡፡ በሳምንቱ ዉስጥ ከፍተኛ የታማሚዎች ቁጥር ሪፖርት ያደረጉ ወረዳዎች ጎምቦራ 213 ፣ምእራብ ባዳዋቾ 203፣ ጊምቢቹ 147 ፣ሾኔ 120፣ ሶሮ 132፣ እና ሾኔ 120 ከፍተኛ የወባ ታማሚዎች ሪፖርት ያደረጉ ወረዳዎች ናቸዉ፡፡ ስለሆነም የወባ መከላከልና መቆጣጠር ስራዎች እንዲሁም የህክምና ተግባራት ተጠናከረዉ መቀጠል ይኖርባቸዋል፡፡
‎አጣዳፊ የምግብ እጥረት (SAM):- በሳምንቱ እንደ ዞን 122 ከ5 ዓመት በታች ታማሚ ህፃናት ሪፖርት የተደረጉ ሲሆን ከባለፈዉ ሳምንት አንፃር ሲታይ ጨምሯል፡፡ ሲራሮ ባዳዋቾ(29) ሶሮ (17)፣ ምስራቅ ባዳዋቾ(16) እና ሾኔ (12) በሳምንቱ ከፍተኛ SAM ሪፖርት ያደረጉ ወረዳዎች ናቸዉ፡፡ በሳምንቱ ዉሰጥ 4 (3%) የተወሳሰበ የምግብ እጥረት የተመዘገበ ሲሆን የቅድመ ምርመራ እና የተመላላሽ ህክምና ተግባራት ተጠናክረዉ መቀጠል አለባቸዉ፡፡ እንዲሁም በቂ ግብዓትና የህክምና ፕሮቶኮል ተጠብቆ በየጤና ተቋማቱ አገልግሎት እንዲሰጥና የመከላከል ተግባራት ላይ ትኩረት ማድረግ ያስፈልጋል ፡፡
‎የመካከለኛ የምግብ እጥረት በተመለከተ ፡- እንደ ዞን 437 ከ5 ዓመት በታች ህፃናትና 182 የሚያጠቡና ነፍሰ ጡር እናቶች ሪፖርት የተደረገ ሲሆን የልየታ ሰራዉ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ መስራት የሚገባዉና IMAM ወረዳዎች ላይ ከአደጋዉ መከላከልና ምግብ ዋስትና ፅ/ቤት ጋር በመሆን የግብዓት አቅርቦት ስራዎች እንዲሰሩ ማድረግ ይገባል፡፡

‎በቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ፡- ከHIV/AIDS እንደ ዞን 2 ከን/ኢ/ሙ/መ/ሆ 1 እና ከ ሆሳዕና 1 ሪፖርት የተደረገ እና አዳዲስ ተጠቂዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ነዉ፡፡ index case ማፈላለግ ፣ ፀረ HIV/AIDS ማስጀመር እና ግንዛቤ /የባህሪይ ለዉጥ ሥራዎችን መስፋት መስራት ያስፈልጋል፡፡
‎ከ TB አንፃር በሳምንቱ 32 ኬዞች የተለዩ ሲሆን በሽታዉ የተገኘባቸዉን መድኃኒት ማሰጀመርና የindex case የማፈላለግ ተግባራት ሊከናወኑ ይገባል፡፡
‎ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ፡- በሳምንቱ እንደ ዞን 12 አዲስ Diabetic Mellitus እና 13 Hypertension ኬዞች ሪፖርት ተደርጓል፡፡በመሆኑም አዳዲስ ኬዞች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ስለሆነ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ መስራት ይገባል፡፡

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ በሀዲያ ዞን የምሥራቅ ባዳዋቾ ወረዳ  " በጎነት ለኢትዮጵያ" ከፍታ በሚል መሪ ቃል የ2017 ዓ/ም የወጣቶች የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ሥራዎች ተከናወነ ።   ****** 0...
11/08/2025

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ በሀዲያ ዞን የምሥራቅ ባዳዋቾ ወረዳ " በጎነት ለኢትዮጵያ" ከፍታ በሚል መሪ ቃል የ2017 ዓ/ም የወጣቶች የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ሥራዎች ተከናወነ ።

****** 03 - 12 - 2017 ዓ/ም *******

የሠዎችን ችግርና ህመም እንደራስ በመረዳት ካሉበት ሁኔታ እንዲወጡ ማገዝ በፈጣሪ ዘንድም ሆነ በሠው የሚያስመስግን ሥራ መሆኑን የገለጹት አቶ ብርሃኑ ሻሜቦ የምሥራቅ ባዳዋቾ ወረዳ አስተዳዳሪ ሲሆኑ፡-

በችግር ላይ ያሉትን ሰዎች መርዳትና ማገዝ የወቅት ጉዳይ ሳይሆን የየዕለት ተግባራችን መሆን ይገባዋል ሲሉ አሳስበዋል።

የዘንድሮ የበጎ አገልግሎት የአዳዲስ ቤቶችን ግንባታ፥ የቤቶች እድሳት፥ የመንገድ ከፈታ፥ የከተማ ጽዳት፥ የችግኝ ተከላ፥ አቅመ ደካሞችን ማገዝ፥ ወላጅ አጥ ልጆችን መርዳትና የመማሪያ መሳሪያዎችን መስጠትና የደም ልገሳንና የገንዘብ ሥጦታ አንደሚያጠቃቅል የገለጹት አቶ እስራኤል ሣንት የወረዳው ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤትኃላፊ የገለጹ ሲሆን፡-

በዚህ የክረምት የበጎ አገልግሎት የሚሰሩ የመልካም ሥራዎች ወደ ገንዘብ ሲቀየር ከ33 ሚሊዮን በላይ መ
ሆኑን ገልጸው በዕለት ከሚደረገው የደም ልገሳ 30 ዩኒት ለመሰብሰብ ታቅዶ 27 ዩኒት መሰብሰብንና ይህም በፐርሰንት ሲቀመጥ ከ90% በላይ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

በዚህ የበጎ አገልግሎት ማስጀመሪያ ላይ አቶ ዓለሙ ጫኪሶ የወረዳው የመንግስት ተጠሪ ፥ አቶ ደምሴ ደዴቦ የወረዳው ምክር ቤት ዋና አፍ-ጉባኤና የወረዳው ፑል አመራር እንዲሁም የወጣቶችና ሴቶች ክንፍ መገኘታቸውን መንግስት ከሙኒኬሽን አስታውቋል።
ምንጭ:-ምስ/ባደዋቾ መ/ኮሚኒኬሽን
ሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ

በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በዞናችን በሁሉም ጤና ተቋማት የችግኝ ተከላና ሌሎች የክረምት በጎ ተግባራት በሥፋት ተከናወነ።‎                  *********24/11/201...
31/07/2025

በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በዞናችን በሁሉም ጤና ተቋማት የችግኝ ተከላና ሌሎች የክረምት በጎ ተግባራት በሥፋት ተከናወነ።
‎ *********24/11/2017******
‎በዛሬው ዕለት በተከናወነው የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ ወቅት በጤና ተቋማት ላይ የችግኝ ተከላ፣የደም ልገሣ፣የተለያዩ ጤና ምርመራዎች እና ለአቅመ ደካሞች ድጋፍ የማድረግ ተግባራት በሥፋት ተከናውነዋል።

‎የዞን ጤና መምሪያ ሀላፊ ዶ/ር ደሣለኝ ሹጉጤ የአርንጓዴ አሻራቸውን በምዕራብ ሶሮ በመገኘት የከናወኑ ሲሆን በወቅቱም ሁሉንም ችግኞች እንክብካቤ ማድረግ ተገቢ መሆኑን ጠቅሰው በተለይም በጤና ተቋማት የተተከሉትን ችግኞች ተቋማቱ በባለቤትነት ልከታተሉ እንደምገባ ጠቁመው ሌሎች የክረምት በጎ ተግባራትም የበለጠ ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አሳስበዋል።
‎ የሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ!!

Address

Hosa'ina

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ/Hadiya Zone Health Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram