Jimma University - Institute of health

Jimma University - Institute of health To give latest information for our society

ሴቶችን ለአመራርነት ለማብቃት የሚደረጉ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የጅማ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኢንስቲትዩት ገለጸ ።ጤና ኢንስቲትዩት ፡ ሚያዝያ 19 ቀን /2014 ዓ.ም ************* ...
28/04/2022

ሴቶችን ለአመራርነት ለማብቃት የሚደረጉ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የጅማ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኢንስቲትዩት ገለጸ ።
ጤና ኢንስቲትዩት ፡ ሚያዝያ 19 ቀን /2014 ዓ.ም
*************
ሴቶችን ለአመራርነት ለማብቃት የሚስችል ሥልጠናም ተሰጥቷል፡፡
ሥልጠናዉን በንግግር የከፈቱት የጅማ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኢንስቲትዩት የአስተዳደር እና ልማት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ዝናሽ ሠለሞን እንዳሉት፤ ሴቶችን በማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ዘርፎች ለማብቃት የሚደረጉ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል ።
በዋናነት የሴቶች ተሳታፊነት እና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥና ሴቶችን ለኃላፊነት ለማብቃት እየተደረገ ባለዉ ጥረት ዉስጥ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ገልጸዉ ከዚህ በተሻለ መልኩ ዉጤት ለማስመዝገብ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎችን መስጠት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አክለዉም፤ ሴቶች ለኃላፊነት ደረጃ ራሳቸዉን ለማብቃት ጥረት በማድረግ ለዉጤታማነት መትጋት እንዳለባቸዉ ጠቅሰዉ በየጊዜዉ ሴቶችን ለማብቃት የሚሰጡ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎችን ወደ ተግባር በመቀየር ሊቀዉ መገኘት እንዳለባቸዉም አሳስበዋል።
የሴቶችን የአመራርነት አቅም ማጎልበቻ ዙሪያ የጥናታዊ ጽሁፍ በማቅረብ ሥልጠና የሰጡት አቶ ታደለ ማሞ ናቸዉ፡፡
አቶ ታደለ ማሞ ሥልጠናዉን በሰጡበት ወቅት እንዳሉት፤ ሴቶችን ማብቃት እና ደህንነታቸውን ለማስጠብቅ ሁሉም አካል የግልና የጋራ ኃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
ሴቶችን ከማብቃት አኳያ በርካታ ተግዳሮቶች እንደሚያጋጥሙ ጠቅሰዉ ችግሮቹን ለመከላከልና ለመቀነስ እንዲሁም ያላቸውን እምቅ ችሎታ እንዲያወጡና አስተዋጽኦቸውን ማበርከት እንዲችሉ ለማብቃት ጥረት ማድረግ ተገቢ መሆኑን ገልጸዋል።
ለአብነትም ያደጉ ሀገራት በቅድሚያ በሴቶች እና በህጻናት ላይ ዉጤት ለማስመዝገብ እንደሚሰሩ ጠቅሰዉ በማህበረሰባችን ዘንድ ለሴቶች የሚሰጠዉን ዝቅተኛ አመለካከት በመቅረፍ በማንኛውም የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት ውስጥ የመሳተፍ እድላቸዉን አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ብለዋል፡፡
በቀጥይም የሴቶችን የአመራር ሰጭነት ሚና ለማሳደግ በአቅም ግንባታ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም አቶ ታደለ ማሞ አስረድተዋል፡፡
በሥልጠናዉ ላይ ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኢንስቲትዩት የተዉጣጡ ሴት ሰራተኞች ተሳትፈዋል፡፡Telegram:- https://t.me/juihealth

Jimma University-Institute of Health and its Environment*********************   26/04/2022Institute of Health constitute...
26/04/2022

Jimma University-Institute of Health and its Environment
********************* 26/04/2022
Institute of Health constitutes faculty of Medicine, faculty of public health, faculty of health sciences, and Jimma Medical centre.
Among of this jimma university medical center is one of the country's leading medical institutions serving more than 20 million people in southwestern Ethiopia and patients from neighboring countries with state-of-the-art facilities. The Center is one of the six hospitals selected to provide radiation therapy in the country. It also has an oncology centre, and oxygen production plant, and a biomedical centre that serves 12 operating rooms, 800 inpatient beds, and 12 intensive care units. The building complex has a helicopter landing space for medical tourism. Because of its international standards, JU medical centre can efficiently treat patients who travel from neighboring countries searching for better treatment.
The Oncology unit at JUMC was established since June 2011 E.C starting its’ medical Oncology (Chemotherapy) services, Referral for chemotherapy reduced by 97% .This offer Special appreciation and gratitude to the staff team, Institute management and surgical GI Oncology team. Like, share and comment.
Telegram: - https://t.me/juihealth

ከ33 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የተደረገባቸው የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ።ጤና ኢንስቲትዩት ፡ ሚያዝያ 16 ቀን /2014 ዓ.ም *************ሂዩማን ብሪጅ የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅ...
24/04/2022

ከ33 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የተደረገባቸው የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ።
ጤና ኢንስቲትዩት ፡ ሚያዝያ 16 ቀን /2014 ዓ.ም
*************
ሂዩማን ብሪጅ የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት 33 ሚሊዮን 5 መቶ ሺ ብር ወጭ የተደረገባቸው የሕክምና ባለሙያዎች የስራ ላይ ደህንነት መጠበቂያ ቁሳቁስ/plastic apron/ ነዉ ለጅማ ህክምና ማዕከል ድጋፍ ያደረገዉ።
የጅማ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኢንስቲትዩት ም/ፕሬዚዳንት ዶር ኤሊያስ አሊ በድጋፍ ርክክብ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ እንዳሉት ፤ በአሁኑ ወቅት የጤና አገልግሎት አሰጣጡን በማሻሻል እና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተደረገ ባለዉ እንቅስቃሴ ዉስጥ የግብረ ሰናይ ድርጅቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ለአብነትም ሂዩማን ብሪጅ የተሰኘ የሲዊድን ሀገር ግብረ ሰናይ ድርጅት ያደረገው በጎ ተግባር የሆስፒታሉን ስራ በማቀላጠፍ ለህብረተሰቡ መሰረታዊ ጤና አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያግዝ ገልጸዉ ላደረገው ድጋፍም ምስጋና አቅርበዋል።
እንደ ዶር ኤሊያስ አሊ ገለጻ፤ ይህንን ቁሳቁስ በከፊል በጅማ እና አካባቢዉ ለሚገኙ የጤና ተቋማት በማከፋፈል ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንድሰጥ ይደረጋል ብለዋል፡፡
በሆስፒታሉ የፋርማሲ ክፍል ዳይሬክተር አቶ አወል አባገሮ በበኩላቸው ድርጅቱ 234ሺ የሕክምና ባለሙያዎች የስራ ላይ ደህንነት መጠበቂያ ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉን ጠቅሰዉ ይህ ቁሳቁስ ለሁለት ዓመታት ያክል አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።
አሁን በድጋፍ የተገኘዉ የባለሙያዎች ንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁስ ከዚህን በፊት የሚስተዋለዉን የቁሳቁስ እጥረት ችግሮችን በመቅረፍ የተሻለ የሕክምና አገልግሎት ለመስጠት እንደሚረዳም ተናግረዋል።Telegram:- https://t.me/juihealth

የጅማ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኢንስቲትዩት የአስተዳደር እና ልማት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ዝናሽ ሠለሞን ለፋሲካ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ::ጅማ ጤና ኢንስቲትዩት ፡ 15/08/20...
23/04/2022

የጅማ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኢንስቲትዩት የአስተዳደር እና ልማት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ዝናሽ ሠለሞን ለፋሲካ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ::
ጅማ ጤና ኢንስቲትዩት ፡ 15/08/2014 ዓ.ም
*********************************************
ለመላው የክርስትና ኃይማኖት ተከታዮች “እንኳን ለትንሳዔ በዓል በሰላም አደረሳችሁ”ባሉበት መልዕክታቸው፤ በዓሉ የክርስትና እምነት ተከታዮች እርስ በእርስ ግንኙነታቸውን የበለጠ የሚያጠናክሩበት፣ የአብሮነትና የመረዳዳት እሴቶቻቸውን የሚያዳብሩበት፣ ተቻችለውና ተከባብረው በጋራ በዓሉን በማክበር መተሳሰብን የሚያሳዩበት ታላቅ በዓል ነው፡፡
የትንሳዔ በዓል በክርስትና ዕምነት ተከታዮች ዘንድ ትልቅ ትርጉም እና ስፍራ ያለው መሆኑን በመግለጽ፤ ለዚህ ታላቅ ክብረ በዓል በሰላም በመድረሳችሁ፤ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለሁ ብለዋል።
ህብረተሰቡ በእምነቱ ሳይለያይ ችግሩንምሆነ ደስታውን አብሮ በማሳለፍ በአንድነት የሚኖር መሆኑን ከሚያሳይባቸው አጋጣሚዎች አንዱ እንደትንሳኤ በዓል ያሉ ታላላቅ በዓላት መሆናቸውን የአስተዳደር እና ልማት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ዝናሽ ሠለሞን አመልክተዋል።
በዓሉን በቤት ውስጥ በምናከብርበት ወቅትም እንደወትሮው መሰባሰብ ሳይበዛ አስፈላጊውን ጥንቃቄ በማድረግ ብሎም የተቸገሩ ወገኖቻችንን በማሰብ ሊሆን እንደሚገባ አስገንዘበዋል።
በዓሉ በሚፈጥረው መልካም አጋጣሚ ወገናዊ መተሳሰብ እና መደጋገፍ የሚነግስበት እንዲሆን ከልብ እመኛለሁ” በማለትም ገልጸዋል።
በመጨረሻም በዓሉ የሠላም፣ የፍቅር፣ የደስታ፣ የመተሳሰብ እና የአንድነት እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡Telegram:- https://t.me/juihealth
Daarektarri ol'aanaan bulchiinsaa fi misooma Inistitiyuutii fayyaa Yuunivarsiitii Jimmaa, Aadde Zinnaash Salamoon, erga baga geessaanii ayyaana Faasikaa hordoftoota amantaa Kiristaanaaf dabarsanii jiru.
Inistitiyuutii Fayya: ፡ 15/08/2014
*******************************
Hordoftoota amantaa Kiristaanaaf ergaa ayyaana Faasikaa baga nagaan geessaanii wayita dabarsanitti,"ayyaanichi hordooftoota amantaa Kiristaanaa walitti dhufeenya isaanii daran kan cimsu, duudhaalee waliin jireenyaa fi wal gargaaruu kan dagaagsu, wal dandawuu fi wal kabajuun, waliif yaadaa kan waliin dabarsan ayyaana guddaadha" jedhaniiru.
Ayyaanni Faasikaa hordoftoota amantaa Kiristaanaa biratti hiikaa fi bakka guddaa kan qabu ta'uu eeranii, ayyaana guddaa kanas nagaan gahuu keessaniif baga gammaddanis jedhaniiru.
Carraawwaan hawaasni amantaan osoo gargar hinbahin,rakkoos ta'ee makkoo waliin dabarsuun, tokkumaan waliin jiraatan ibsan keessaa tokko ayyaanota gurguddoo akka Faasikaa ta'uu, Daarektarri olaanaan bulchiinsaa fi misoomaa, Aadde Zinnaash Salamoon ibsanii jiru.
Ayyaanicha yeroo kabajnus akkuma baratame walitti qabamiinsi osoo hinbaay'atin of eeggannoo barbaachisu taasisuun, lammiilee rakkatanis yaadachuun ta'uu akka qabu hubachiisaniiru.
"Hiree gaarii ayyaanichi uumunis aantummaan walii yaaduu fi wal gargaaruu kan itti dagaagu akka ta'us Onnee koorraan hawwa"jechuunis ibsaniiru.
Dhumarrattis, ayyaanichi kan nagaa, jaalalaa, gammachuu,kan walii yaaduufi kan tokkummaa akka ta'u hawwii dansaa qaban ibsanii jiru.Telegram: - https://t.me/juihealth

12/04/2022

Address

Jimma
Jimma
NO

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Jimma University - Institute of health posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Jimma University - Institute of health:

Share