Jimma University - Institute of health

Jimma University - Institute of health To give latest information for our society

ሴቶችን ለአመራርነት ለማብቃት የሚደረጉ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የጅማ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኢንስቲትዩት ገለጸ ።ጤና ኢንስቲትዩት ፡ ሚያዝያ 19 ቀን /2014 ዓ.ም ************* ...
28/04/2022

ሴቶችን ለአመራርነት ለማብቃት የሚደረጉ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የጅማ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኢንስቲትዩት ገለጸ ።
ጤና ኢንስቲትዩት ፡ ሚያዝያ 19 ቀን /2014 ዓ.ም
*************
ሴቶችን ለአመራርነት ለማብቃት የሚስችል ሥልጠናም ተሰጥቷል፡፡
ሥልጠናዉን በንግግር የከፈቱት የጅማ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኢንስቲትዩት የአስተዳደር እና ልማት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ዝናሽ ሠለሞን እንዳሉት፤ ሴቶችን በማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ዘርፎች ለማብቃት የሚደረጉ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል ።
በዋናነት የሴቶች ተሳታፊነት እና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥና ሴቶችን ለኃላፊነት ለማብቃት እየተደረገ ባለዉ ጥረት ዉስጥ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ገልጸዉ ከዚህ በተሻለ መልኩ ዉጤት ለማስመዝገብ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎችን መስጠት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አክለዉም፤ ሴቶች ለኃላፊነት ደረጃ ራሳቸዉን ለማብቃት ጥረት በማድረግ ለዉጤታማነት መትጋት እንዳለባቸዉ ጠቅሰዉ በየጊዜዉ ሴቶችን ለማብቃት የሚሰጡ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎችን ወደ ተግባር በመቀየር ሊቀዉ መገኘት እንዳለባቸዉም አሳስበዋል።
የሴቶችን የአመራርነት አቅም ማጎልበቻ ዙሪያ የጥናታዊ ጽሁፍ በማቅረብ ሥልጠና የሰጡት አቶ ታደለ ማሞ ናቸዉ፡፡
አቶ ታደለ ማሞ ሥልጠናዉን በሰጡበት ወቅት እንዳሉት፤ ሴቶችን ማብቃት እና ደህንነታቸውን ለማስጠብቅ ሁሉም አካል የግልና የጋራ ኃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
ሴቶችን ከማብቃት አኳያ በርካታ ተግዳሮቶች እንደሚያጋጥሙ ጠቅሰዉ ችግሮቹን ለመከላከልና ለመቀነስ እንዲሁም ያላቸውን እምቅ ችሎታ እንዲያወጡና አስተዋጽኦቸውን ማበርከት እንዲችሉ ለማብቃት ጥረት ማድረግ ተገቢ መሆኑን ገልጸዋል።
ለአብነትም ያደጉ ሀገራት በቅድሚያ በሴቶች እና በህጻናት ላይ ዉጤት ለማስመዝገብ እንደሚሰሩ ጠቅሰዉ በማህበረሰባችን ዘንድ ለሴቶች የሚሰጠዉን ዝቅተኛ አመለካከት በመቅረፍ በማንኛውም የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት ውስጥ የመሳተፍ እድላቸዉን አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ብለዋል፡፡
በቀጥይም የሴቶችን የአመራር ሰጭነት ሚና ለማሳደግ በአቅም ግንባታ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም አቶ ታደለ ማሞ አስረድተዋል፡፡
በሥልጠናዉ ላይ ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኢንስቲትዩት የተዉጣጡ ሴት ሰራተኞች ተሳትፈዋል፡፡Telegram:- https://t.me/juihealth

Jimma University-Institute of Health and its Environment*********************   26/04/2022Institute of Health constitute...
26/04/2022

Jimma University-Institute of Health and its Environment
********************* 26/04/2022
Institute of Health constitutes faculty of Medicine, faculty of public health, faculty of health sciences, and Jimma Medical centre.
Among of this jimma university medical center is one of the country's leading medical institutions serving more than 20 million people in southwestern Ethiopia and patients from neighboring countries with state-of-the-art facilities. The Center is one of the six hospitals selected to provide radiation therapy in the country. It also has an oncology centre, and oxygen production plant, and a biomedical centre that serves 12 operating rooms, 800 inpatient beds, and 12 intensive care units. The building complex has a helicopter landing space for medical tourism. Because of its international standards, JU medical centre can efficiently treat patients who travel from neighboring countries searching for better treatment.
The Oncology unit at JUMC was established since June 2011 E.C starting its’ medical Oncology (Chemotherapy) services, Referral for chemotherapy reduced by 97% .This offer Special appreciation and gratitude to the staff team, Institute management and surgical GI Oncology team. Like, share and comment.
Telegram: - https://t.me/juihealth

ከ33 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የተደረገባቸው የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ።ጤና ኢንስቲትዩት ፡ ሚያዝያ 16 ቀን /2014 ዓ.ም *************ሂዩማን ብሪጅ የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅ...
24/04/2022

ከ33 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የተደረገባቸው የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ።
ጤና ኢንስቲትዩት ፡ ሚያዝያ 16 ቀን /2014 ዓ.ም
*************
ሂዩማን ብሪጅ የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት 33 ሚሊዮን 5 መቶ ሺ ብር ወጭ የተደረገባቸው የሕክምና ባለሙያዎች የስራ ላይ ደህንነት መጠበቂያ ቁሳቁስ/plastic apron/ ነዉ ለጅማ ህክምና ማዕከል ድጋፍ ያደረገዉ።
የጅማ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኢንስቲትዩት ም/ፕሬዚዳንት ዶር ኤሊያስ አሊ በድጋፍ ርክክብ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ እንዳሉት ፤ በአሁኑ ወቅት የጤና አገልግሎት አሰጣጡን በማሻሻል እና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተደረገ ባለዉ እንቅስቃሴ ዉስጥ የግብረ ሰናይ ድርጅቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ለአብነትም ሂዩማን ብሪጅ የተሰኘ የሲዊድን ሀገር ግብረ ሰናይ ድርጅት ያደረገው በጎ ተግባር የሆስፒታሉን ስራ በማቀላጠፍ ለህብረተሰቡ መሰረታዊ ጤና አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያግዝ ገልጸዉ ላደረገው ድጋፍም ምስጋና አቅርበዋል።
እንደ ዶር ኤሊያስ አሊ ገለጻ፤ ይህንን ቁሳቁስ በከፊል በጅማ እና አካባቢዉ ለሚገኙ የጤና ተቋማት በማከፋፈል ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንድሰጥ ይደረጋል ብለዋል፡፡
በሆስፒታሉ የፋርማሲ ክፍል ዳይሬክተር አቶ አወል አባገሮ በበኩላቸው ድርጅቱ 234ሺ የሕክምና ባለሙያዎች የስራ ላይ ደህንነት መጠበቂያ ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉን ጠቅሰዉ ይህ ቁሳቁስ ለሁለት ዓመታት ያክል አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።
አሁን በድጋፍ የተገኘዉ የባለሙያዎች ንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁስ ከዚህን በፊት የሚስተዋለዉን የቁሳቁስ እጥረት ችግሮችን በመቅረፍ የተሻለ የሕክምና አገልግሎት ለመስጠት እንደሚረዳም ተናግረዋል።Telegram:- https://t.me/juihealth

የጅማ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኢንስቲትዩት የአስተዳደር እና ልማት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ዝናሽ ሠለሞን ለፋሲካ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ::ጅማ ጤና ኢንስቲትዩት ፡ 15/08/20...
23/04/2022

የጅማ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኢንስቲትዩት የአስተዳደር እና ልማት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ዝናሽ ሠለሞን ለፋሲካ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ::
ጅማ ጤና ኢንስቲትዩት ፡ 15/08/2014 ዓ.ም
*********************************************
ለመላው የክርስትና ኃይማኖት ተከታዮች “እንኳን ለትንሳዔ በዓል በሰላም አደረሳችሁ”ባሉበት መልዕክታቸው፤ በዓሉ የክርስትና እምነት ተከታዮች እርስ በእርስ ግንኙነታቸውን የበለጠ የሚያጠናክሩበት፣ የአብሮነትና የመረዳዳት እሴቶቻቸውን የሚያዳብሩበት፣ ተቻችለውና ተከባብረው በጋራ በዓሉን በማክበር መተሳሰብን የሚያሳዩበት ታላቅ በዓል ነው፡፡
የትንሳዔ በዓል በክርስትና ዕምነት ተከታዮች ዘንድ ትልቅ ትርጉም እና ስፍራ ያለው መሆኑን በመግለጽ፤ ለዚህ ታላቅ ክብረ በዓል በሰላም በመድረሳችሁ፤ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለሁ ብለዋል።
ህብረተሰቡ በእምነቱ ሳይለያይ ችግሩንምሆነ ደስታውን አብሮ በማሳለፍ በአንድነት የሚኖር መሆኑን ከሚያሳይባቸው አጋጣሚዎች አንዱ እንደትንሳኤ በዓል ያሉ ታላላቅ በዓላት መሆናቸውን የአስተዳደር እና ልማት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ዝናሽ ሠለሞን አመልክተዋል።
በዓሉን በቤት ውስጥ በምናከብርበት ወቅትም እንደወትሮው መሰባሰብ ሳይበዛ አስፈላጊውን ጥንቃቄ በማድረግ ብሎም የተቸገሩ ወገኖቻችንን በማሰብ ሊሆን እንደሚገባ አስገንዘበዋል።
በዓሉ በሚፈጥረው መልካም አጋጣሚ ወገናዊ መተሳሰብ እና መደጋገፍ የሚነግስበት እንዲሆን ከልብ እመኛለሁ” በማለትም ገልጸዋል።
በመጨረሻም በዓሉ የሠላም፣ የፍቅር፣ የደስታ፣ የመተሳሰብ እና የአንድነት እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡Telegram:- https://t.me/juihealth
Daarektarri ol'aanaan bulchiinsaa fi misooma Inistitiyuutii fayyaa Yuunivarsiitii Jimmaa, Aadde Zinnaash Salamoon, erga baga geessaanii ayyaana Faasikaa hordoftoota amantaa Kiristaanaaf dabarsanii jiru.
Inistitiyuutii Fayya: ፡ 15/08/2014
*******************************
Hordoftoota amantaa Kiristaanaaf ergaa ayyaana Faasikaa baga nagaan geessaanii wayita dabarsanitti,"ayyaanichi hordooftoota amantaa Kiristaanaa walitti dhufeenya isaanii daran kan cimsu, duudhaalee waliin jireenyaa fi wal gargaaruu kan dagaagsu, wal dandawuu fi wal kabajuun, waliif yaadaa kan waliin dabarsan ayyaana guddaadha" jedhaniiru.
Ayyaanni Faasikaa hordoftoota amantaa Kiristaanaa biratti hiikaa fi bakka guddaa kan qabu ta'uu eeranii, ayyaana guddaa kanas nagaan gahuu keessaniif baga gammaddanis jedhaniiru.
Carraawwaan hawaasni amantaan osoo gargar hinbahin,rakkoos ta'ee makkoo waliin dabarsuun, tokkumaan waliin jiraatan ibsan keessaa tokko ayyaanota gurguddoo akka Faasikaa ta'uu, Daarektarri olaanaan bulchiinsaa fi misoomaa, Aadde Zinnaash Salamoon ibsanii jiru.
Ayyaanicha yeroo kabajnus akkuma baratame walitti qabamiinsi osoo hinbaay'atin of eeggannoo barbaachisu taasisuun, lammiilee rakkatanis yaadachuun ta'uu akka qabu hubachiisaniiru.
"Hiree gaarii ayyaanichi uumunis aantummaan walii yaaduu fi wal gargaaruu kan itti dagaagu akka ta'us Onnee koorraan hawwa"jechuunis ibsaniiru.
Dhumarrattis, ayyaanichi kan nagaa, jaalalaa, gammachuu,kan walii yaaduufi kan tokkummaa akka ta'u hawwii dansaa qaban ibsanii jiru.Telegram: - https://t.me/juihealth

12/04/2022
ጅማ ዩኒቨርስቲ የዉስጥ ደዌ ትምህርት ክፍል የልብ ህክምና ዩኒት  ለካርዲዮሎጂ ሰብስፔሻሊቲ ተማሪዎች ፈረንሳይ ሃገር  እና አዲስ አበባ ከሚገኙ የልብ ህክምና ተቌማት ጋር በመተባበር ሥልጠና ...
09/04/2022

ጅማ ዩኒቨርስቲ የዉስጥ ደዌ ትምህርት ክፍል የልብ ህክምና ዩኒት ለካርዲዮሎጂ ሰብስፔሻሊቲ ተማሪዎች ፈረንሳይ ሃገር እና አዲስ አበባ ከሚገኙ የልብ ህክምና ተቌማት ጋር በመተባበር ሥልጠና መስጠት ጀመረ።
ጤና ኢንስቲትዩት ፡ ሚያዚያ 01 /2014 ዓ.ም
*************
ጅማ ዩኒቨርስቲ የዉስጥ ደዌ ትምህርት ክፍል የልብ ህክምና ዩኒት ለካርዲዮሎጂ ሰብስፔሻሊቲ ተማሪዎች ፈረንሳይ ሃገር ከሚገኘው ሴንት ጆሴፍ- ሴንት ሉክ ሆስፒታል ጋር በመተባበር ስልጠና በመስጠት ላይ ይገኛል።
ከ "የልብ ማዕከል በኢትዮዽያ" ጋር በመተባበር ለ30 ሰዎች የተሳካ የልብ ህክምና እና ምርመራ አገልግሎትም ተሰጥቷል።
የዚሁ ትብብር አካል የሆነው እና ለሁለት ሳምንታት በአዲስ አበባ የልብ ማዕከል በጥምረት በተካሄደው የልብ ህሙማንን የመመርመር እና የማከም ስራ ከ 30 በላይ ለሚሆኑ የልብ እና የልብ ደምስር ህመም (Coronary Artery Disease) ላለባቸው ህሙማን ምርመራ እና ህክምና (Coronary Angiography and stenting/PCI) ማድረግ ተችሏል።
ከዚሁ ጎን ለጎን በሃገር ውስጥ ለማግኘት የሚያስቸግሩ እና ዉድ የሆኑ ለዚሁ ህክምና የሚውሉ አላቂ እቃዎችን (Coronary stents, coronary catheters, coronary balloons, etc) ለልብ ህሙማኑ ህክምና እንዲውል በነጻ መለገስ ተችሏል።
የትብብር ፕሮግራሙን የሚመሩት ዶ/ር መሐመድ አባመጫ እንደገለጹት በቀጣይነት የጅማ ዩኒቨርሲቲ፣ የቅዱስ ዻውሎስ ሆስፒታል የልብ ህክምና ዩኒት፣ እና የልብ ማዕከል በኢትዮዽያ በጋራ የት/ት ፕሮግራሙን ለማካሄድ ከመግባባት ላይ መደረሱን ገልጸው ሰልጣኞች በቀጣይ በፈረንሳይ ሃገር በሚገኘው Centre Hospitalier St.Joseph-St.Luc ተከታታይ ትምህርት እና ስልጠናዎች እንደሚሰጧቸው ይፋ አድርገዋል።
Yunivarsiitii Jimmaatti Muummeen kutaa Yaala Keessoo Jila Hospitaala Seent Jooseef-Seent kan Biyya Faransaayiitti Argamu Waliin Ta’uundhaan Ispeeshaalitii Barnoota Kaardiwoolojii Kennuu Eegale.
Barnoota qabatamaa waliin walqabachuudhaan tajaajila yaala fi qorannoo onnee milkaa’e “Wiirtuu Onnee Itoophiyaa” waliin ta’uudhaan raawwateera.
Barnoonni ispeeshaalitii kaardiwoolojii yunivarsiitii Jimmaatti muummee kutaa yaala keessoo biyya Faransaayitti argamuu fi dhaabbilee yaala onnee Finfinneetti argaman waliin ta’uundhaan kennama.
Qaamuma waliigaltee kanaa kan ta’ee fi torbeewwan lamaaf giddugala yaala onnee Finfinneetti yaala dhukkubsattoota onnee hojii qorachuu fi yaaluu walootiin yaalli dhukkubsattoota dhukkuba onnee fi hidda dhiiga onnee (Coronary Artery Disease) qaban namoota 30 ol ta’aniif qorannaa fi yaalii (Coronary Angiography and stenting/PCI) taasisuun danda’ameera.
Kanumaan cinaatti, argachuudhaaf kan dandeessisuu fi meeshaalee dhumatoo yaalii dhukkubsattoota onneetiif oolan kan qaalii ta’an (Coronary stents, coronary catheters, coronary balloons, etc) tolan arjoomuun danda’ameera.
Sagantaa waloo kana kan geggeessan Dr. Mahaammad Abbaamaccaa akka ibsanitti, ittifufinsaan yunivarsiitiin Jimmaa, hospitaalli Qiddus Paawuloos kutaa yaala onnee fi giddugalli onnee Itoophiyaa sagantaa muummichaa geggeessuudhaaf waliigalteerra gahuusaa eeruun leenjitoonni yeroo itti aanutti giddugala biyya Faransaayitti kan argamu ‘Centre Hospitalier St.Joseph-St.Luc’ barnoonnii fi leenjiin ittifufinsaa akka isaaniif kennamu ifoomsaniiru.
Cardiology Sub-specialty training program started at Jimma University Institute of health- a successful joint mission conducted at the Cardiac centre Ethiopia:
The Cardiac unit at the Department of Internal Medicine, Jimma University, has started Cardiology Sub-Specialty training Program in collaboration with Center Hospitalier-St.Joseph-St.Luc, Lyon, France.
The program will be run with close ties between Jimma University, Cardiac center Ethiopia, and, the Cardiac unit of St.Paul hospital in Addis Ababa, Ethiopia.
As part of this collaboration, a joint mission with a team from France, Jimma University, and the Cardiac centre-Ethiopia in Addis Ababa was conducted for two weeks with the aim of training Cardiology fellows from Jimma university. The mission successfully conducted Coronary angiography and stenting (PCI) for over 30 patients with donation of some supplies (stents, coronary catheters, and, angiography balloons) to the centre. The program focuses on exhaustively and cost-effectively utilizing the potentials available both at home and at partner institutions in France to conduct such advanced and costly programs. Telegram:- https://t.me/juihealth

የጅማ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኢንስቲትዩት ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1443ኛው ታላቁ የረመዳን ወር በሰላም አደረሳችሁ ይላል! የረመዳን ወር የመረዳዳት፣ የመተጋገዝና የመከባበሪያ...
02/04/2022

የጅማ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኢንስቲትዩት ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1443ኛው ታላቁ የረመዳን ወር በሰላም አደረሳችሁ ይላል! የረመዳን ወር የመረዳዳት፣ የመተጋገዝና የመከባበሪያ ወር እንዲሆንላችሁም ምኞቱን ይገልጻል!
Hordoftoota Amantaa Islaamaa Maraan Baga Soomaana Ramadaanaa Waggaa 1443 'n isiniin gahe!

የጤናውን ሴክተር አመራሮች አቅም በማጎልበት የህብረተሰቡን የጤና አገልግሎት ማሳደግና ፍላጎት ማሟላት የሚያስችል ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ የጅማ አደጋ ጊዜ ክወና ገለጸ።ጤና ኢንስቲትዩት...
30/03/2022

የጤናውን ሴክተር አመራሮች አቅም በማጎልበት የህብረተሰቡን የጤና አገልግሎት ማሳደግና ፍላጎት ማሟላት የሚያስችል ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ የጅማ አደጋ ጊዜ ክወና ገለጸ።
ጤና ኢንስቲትዩት ፡ መጋቢት 21 /2014 ዓ.ም
*************
ከጅማ ዞን ወረዳዎች እና ከጅማ ህክምና ማዕከል ለተውጣጡ የጤናዉ ሴክተር አመራሮች የክህሎት ማዳበሪያ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል፡፡
የጅማ አደጋ ግዜ ክወና ማዕከል ሀላፊ አቶ ተመስገን ቃበታ የስልጠናው አላማ የጤናዉ ሴክተር አስተዳደራዊ ሂደቱን በማዘመን የህብረተሰቡን የጤና ችግር ከመሰረቱ መፍታት የሚችል ብቁና የሰለጠነ አመራር ማፍራት ነው ብለዋል።
ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን የህብረተሰቡን መሠረታዊ የጤና አገልግሎት ለማሳደግ ከህክምና አገልግሎት በተጨማሪ የጤናው ሴክተር አመራሮችን አቅም ማጎልበት ላይ በትኩረት መስራት አስፈላጊ መሆኑንም አቶ ተመስገን ቃበታ ጨምረው ተናግረዋል፡፡
የጅማ አደጋ ግዜ ክወና ማዕከል ምክትል ሀላፊ አቶ ፈይሳ ማማ በበኩላቸው፤የጤና ስርዓቱ ውጤታማ እንዲሆን ብቃትና ችሎታ ባለው አመራር መመራት ስለሚገባው በተከታታይነት በየደረጃዉ የሚገኙ አመራሮችን የማብቃት ስራ ይቀጥላል ብለዋል፡፡
አክለውም፤የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ሂደት በእውቀትና ጥራት ላይ የተመሰረተ እንዲሆን በማድረግ በህብረተሰቡ ውስጥ የጤና ችግሮችን በጥናትና ምርምር ጭምር በመለየት መፍትሄ ማመንጨት የሚችል የዘርፉ አመራር ማፍራት እንደሚያስፈልግም አስረድተዋል።
አያይዘውም፤ የጤና አገልግሎት ጥራትን ለማሻሻልና የቁጥጥር ስርዓቱን ለማዘመን እንዲቻል ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
ለሶስት ቀናት በሚቆየው ስልጠና ላይ የጅማ ዞን ሁሉም ወረዳዎች እና የጅማ ህክምና ማዕከል የጤናዉ ሴክተር አመራሮች እየተሳተፉ ነው፡፡

የጅማ ህክምና ማዕከል ከጅማ እና አካባቢው ማህበረሰብ ጋር በጤና አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ውይይት አካሂዷል።ጤና ኢንስቲትዩት ፡ መጋቢት 21 /2014 ዓ.ም *************ውይይቱ በማህ...
30/03/2022

የጅማ ህክምና ማዕከል ከጅማ እና አካባቢው ማህበረሰብ ጋር በጤና አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ውይይት አካሂዷል።
ጤና ኢንስቲትዩት ፡ መጋቢት 21 /2014 ዓ.ም
*************
ውይይቱ በማህበረሰቡ እና በህክምና ማዕከሉ ያሉ ችግሮችን በመለየት የጋራ መግባባትን በመፍጠርና የጤና አገልግሎት እንዲሻሻል ለማድረግ ያግዛል ተብሏል።
በውይይቱ የህክምና ማዕከሉ የስድስት ወራት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት በቺፍ ክሊኒካል ዳይሬክተሯ ዶ/ር ፈቲያ አወል ቀርቧል።
የህክምና ማዕከሉ የደባርቅ፣ አፋር የሚገኝ ሆስፒታል፣ ደላንታ፣ ሸነን ጊቤ ሆስፒታሎች እንዲሁም በከፍተኛ ሁለት ጤና ጣቢያ በእውቀት፣ በህክምና ቁሳቁስ እና በሠው ሃይል የማደራጀትና አቅም የመገንባት ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝም በሪፖርቱ ተገልፅዋል።
በተጨማሪም በህክምና ማዕከሉ በኢንተርኔት የተደገፈ የድረ-ገፅ ሪፈራል ዘዴ፣ የተደራጀ ህክምና መረጃ እያያዝ ስርዓት ተዘርግተው እየተሰራባቸው ሲሆን በቅርቡ የተጀመሩ እንደ ካንገት በላይ ህክምና፣ የአዕምሮ ህክምና፣ የጨረር ህክምና፣ የአስክሬን ምርመራ፣ ነፃ የጉበት ቫይረስ ህክምና ያሉ አገልግሎቶች ውጤት እያመጡ መሆናቸው ተነግሯል።
የውስጥ ገቢን በማሳደግ ረገድ ባለፉት ስድስት ወራት ከ13 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ የተደረገ ሲሆን በ2013 ዓ.ም ከተሰበሰበው ገቢ ጋር ሲነፃፀር 80 በመቶ ያህል ነው ተብሏል።
የአገልግሎት አሰጣጥ መጨናነቅና ወረፋን ለመቀነስ የምሳ ሰዓትን ጨምሮ እስከ ምሸት ሁለት ሰዓት ድረስ የህክምና አገልግሎት እንዲሰጥ መደረጉም ተገልፅዋል።
አንዳንድ የህክምና ባለሙያዎች የስነ-ምግባር ጉድለቶች፣ የእጅ ጉዋንትና የመድሃኒት እጥረት፣ ላቦራቶሪና ኤክስሬይ ከማዕከሉ ውጪ አሰሩ ማለት፣ ቀድመው የመጡ ታካሚዎችን ቅድሚያ አለመስጠት፣ ወረፋ፣ የአገልግሎት መጨናነቅ እና የመሳሰሉት ከተወያዮች የተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ናቸው።
ከማህበረሰቡ ጋር የተደረገውን ውይይት የመሩት የጤና ኢንስቲትዩት ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ኤልያስ አሊ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ በሰጡበት ወቅት የግዢ ስርዓት ችግር፣ የቁሳቁስና መድሃኒት ስርቆት፣ የህክምና ባለሙያዎች የፍላጎት ግጭት ዋነኛ ችግሮች መሆናቸውን አንስተዋል።
ችግሮቹን ለመቅረፍ የህክምና ባለሙያዎች የምርምርና ፕሮጀክት ስራዎችን እየሰሩ ህክምና ማዕከሉን በአገልግሎትና በአዳዲስ አሰራሮች እየጠቀሙ ራሳቸውንም ማሳደግ የሚችሉበት ስትራቴጂ ተዘጋጅቶ እየተሰራበት መሆኑን ዶ/ር ኤልያስ አሊ አክለዋል።
በጅማ ከተማና ዞን የሚገኙ ሆስፒታሎችን ከፍተኛ የህክምና አገልግሎት እንዲሰጡ አቅማቸውን በማሳደግ የህክምና ማዕከሉ ልዩ የህክምና አገልግሎት እንዲሰጥ በማስቻል እንደ አገልግሎት መጨናነቅና ወረፋ የመሳሰሉ ችግሮችን መቀነስ እንደሚቻል ተወያዮች ጠቁመዋል።
በህክምና ማዕከሉ ውስጥ በተለዮያዩ ዘርፎች የሚፈጸሙ ስርቆት፣ ብልሹ አሰራር እና ከስነ-ምግባር የወጡ አሰራሮችን ለማስተካከል ማህበረሰቡ በማጋለጥ አብሮ እንዲሰራ ጥሪ ቀርቧል።መረጃዉ የጅማ ዩኒቨርሲቲ ነዉ

ደም በመለገስ በደም እጦት ሳቢያ የሚጠፋውን የሰው ህይወት መታደግ የዜግነት ግዴታን መወጣት ነው ሲሉ በጅማ ህክምና ማዕከል በጎ ፈቃደኛ ደም ለጋሾች ገለጹ፡፡ጤና ኢንስቲትዩት ፡ መጋቢት 20 ...
29/03/2022

ደም በመለገስ በደም እጦት ሳቢያ የሚጠፋውን የሰው ህይወት መታደግ የዜግነት ግዴታን መወጣት ነው ሲሉ በጅማ ህክምና ማዕከል በጎ ፈቃደኛ ደም ለጋሾች ገለጹ፡፡
ጤና ኢንስቲትዩት ፡ መጋቢት 20 /2014 ዓ.ም
*************
በጅማ ህክምና ማዕከል ግቢ ዉስጥ ለተከታታይ ለ3 ቀናት የሚቆይ የደም ልገሳ መርሃ ግብር ተጀምሯል፡፡
ዛሬ ደማቸውን ከለገሱት ሠራተኞች መካከል የሜዲካል ዋርድ ነርስ ክፍል ሃላፊ ጋሻሁን አበራ የዜጎችን ሕይወት ለመታደግ የደም ልገሳ መርሃ ግብር ላይ ተሳትፈዉ ደም በመለገሳቸዉ መደሰታቸዉን ጠቅሰዉ በደም እጦት ሳቢያ የሚጠፋውን የሰው ህይወት መታደግ የዜግነት ግዴታን መወጣት ነው ሲሉም ተናግረዋል፡፡
ደም መለገስ ጉዳት የሌለው እና የሰው ህይወት መታደግ የሚያስችል ተግባር በመሆኑ ሌሎችም እንዲለገሱ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ሌላው በጎ ፍቃደኛ ለጋሽ ታጁ መሀመድ በተለያዩ አደጋዎች እና በደም እጥረት ምክንያት የሚሞቱ እናቶችን ሞት ለመቀነስ ደም የመለገስ ባህል ማዳበር አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዉ ስለ ደም ልገሳ ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራ እንዲጠናከር ጠይቀዋል።
በጅማ ደም ባንክ የሶሻል ሞብላይዜሽን ቡድን አስተባባሪ አቶ መኮንን ደሱ እንዳሉት፤ በጅማ ዞን ደማቸውን ለወገናቸው የሚለግሱ በጎ ፍቃደኞች ቁጥር እየተበራከተ ቢመጣም ከፍላጎት ጋር እየተመጣጠነ አለመሆኑን አስረድተዋል፡፡
የጅማ ደም ባንክ በዓመቱ ከ11ሺህ 5መቶ ዩኒት በላይ ደም ከበጎ ፍቃደኞች ለማሰባሰብ ያቀደ ሲሆን እስካሁን ባለዉ አፈጻጸም 6ሺህ ዩኒት ደም ለማሰብሰብ መቻሉን ገልጸዉ የተሰበሰበው ደም ከታቀደው በላይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
እንደ አቶ መኮንን ደሱ ገለጻ፤በየጊዜዉ እየተሰጠ ያለው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ በተወሰነ መልኩ ለውጥ ቢያመጣም የሚፈለገው ደረጀ ላይ ለመድረስ እንዲቻል በቀጣይ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚሰሩም ተናግረዋል፡፡
በጅማ ህክምና ማዕከል የክሊኒካል ቺፍ ዳይሬክተር ዶ/ር ፈቲያ አወል፤ እንዳሉት ሆስፒታሉ 80 ከመቶ የሚሆነዉን ደም ከጅማ ደም ባንክ ስለሚያገኝ በደም እጥረት ጉዳት እንዳይደርስ አስተዋጽዎ እያበረከተ ነው ብለዋል፡፡
አክለዉም፤ሆስፒታሉ ከደም ባንክ የሚያገኘውን ደም በነጻ ደም ለሚያስፈልጋቸው ታካሚዎች እንደሚያቀርብም ጠቅሰዉ ከጅማ ደም ባንክ ጋር በመተባበር በየጊዜዉ የደም ልገሳ መርሃ ግብር በማካሄድ አቅርቦቱን የማሳደግ ሥራ በማከናወን ላይ እንገኛለን ብለዋል፡፡
አያይዘዉም፤የጅማ ህክምና ማዕከል የጨረር ህክምና በመጀመሩ እና ለዚህ ህክምና ደም ስለሚያስፈልግ በቂ ደም መሰብሰብ ግዴታ መሆንኑ ገልጸዉ ለዚህ ለተቀደሰ ዓላማ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ተሳትፎ እንዲያደርግም ጠይቀዋል።
Telegram:- https://t.me/juihealth

“ስትሮክ መንስኤዉ እና መከላከያ ዘዴዉ”በሚል ርዕስ የተዘጋጀ መጽሃፍ በጅማ ዩኒቨርሲቲ ተመረቀ።  ጅማ ጤና ኢንስቲትዩት ፡ መጋቢት 10/2014 ዓ.ም**************************...
19/03/2022

“ስትሮክ መንስኤዉ እና መከላከያ ዘዴዉ”በሚል ርዕስ የተዘጋጀ መጽሃፍ በጅማ ዩኒቨርሲቲ ተመረቀ።
ጅማ ጤና ኢንስቲትዩት ፡ መጋቢት 10/2014 ዓ.ም
*********************************************
በጤና ባለሙያዉ ወጣት ባምላክ አበባዉ ተዘጋጅቶ ለምረቃ የበቃዉ፤ይህ መጽሃፍ የጅማ ህክምና ማዕከል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ተመርቋል፡፡
በምረቃዉ ሥነ-ስርዓቱ ላይ የጅማ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኢንስቲትዩት ም/ፕሬዚዳነት ዶ/ር ኤሊያስ አሊ እንደተናገሩት፤የህብረተሰቡን የጤና ግንዛቤ ለማሳደግ የሚረዳ እና የሚበረታታ ተግባር ነዉ ብለዋል፡፡ባለሞያዎች ለቃጣይ ትውልድ የሚተርፍ ጤናን ለመጠበቅና ለመከላከል የሚያስችል ቁምነገር ለማህበረሰቡ ማበርከት የሚጠበቅ ሰናይ ተግባር ነው ብለዋል።
ወጣት ባምላክ አበባዉ ያበረከተዉ አስተዋጽኡ ከፍተኛ በመሆኑ ምስጋና ይገበዋል ብለዋል፡፡
የጅማ ህክምና ማዕከል የክሊኒካል ቺፍ ዳይሬክተር ዶ/ር ፈቲያ አወልም ባደረጉት ንግግር፤ ይህ መጽሃፍ በየደረጃዉ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ግንዛቤ ለማሳደግ የሚረዳ በመሆኑ ወደ ተለያዩ ቋንቋዎች ተተረጉሞ ለሁሉም ተደራሽ መሆን እንዳለበት ገልጸዋል፡፡
በኢትዮጲያ የነርሶች ማህበር የጅማ ተወካይ መምህር አድማሱ በላይ በበኩላቸዉ፤ አሁን የተመረቀዉ መጽሃፍ ስለስትሮክ መንስኤዉ እና መከላከያ ዘዴዎችን የሚዳስስ ስለሆነ ህብረተሰቡ በቀላሉ አንብቦ ተጠቃሚ ይሆናል ብለዋል፡፡
የህብረተሰቡን የጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተዘጋጀዉ መጽኃፍ ለሌሎችም አርአያ የሚሆን ነዉ ያሉት መምህር አድማሱ የኢትዮጲያ የነርሶች ማህበር ይህንን ተግባር እንደሚያበረታታም ተናግረዋል፡፡
የመጽሃፉ ደራሲ እና የጤና ባለሙያዉ ወጣት ባምላክ አበባዉ ይህንን ለማዘጋጀት ያነሳሳዉ በሥራ አጋጣሚ ካስተዋለዉ ችግር በመነሳት እንደሆነም አሰረድተዋል፡፡
ይህ መጽሃፍ የህብረተሰቡን የጤና ችግሮች ለመቅረፍ የሚረዳ መሆኑን ጠቅሰዉ በቀጠይ ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች ተደራሽ ለማድረግ ዕቅድ እንዳለዉም ተናግረዋል፡፡
በምረቃው ላይ ስለ እስትሮክ በሽታ አጭር ጽሑፍ ያቀረቡት ዶክተር ገላው ሀይለማርያም አንዳብራሩት ስትርክ በድንገት የሚከሰት አንጎል ላይ ደም መፍሰስ መይም የአንጎል የደም ዝውውር መስተጓጎል ነው።
ወደ አንግል የሚሄደው የደም ዝውውር መቋረጥ 87 በመቶ የሚከሰት ሲሆን ቀሪው 13 በመቶ አንጎል ላይ ደም በመፍሰስ ነው ያሉት ዶር ገላው የዚህ አይነቱ እስትሮክ ብዙውን ጊዜ ለሞት አጋላጭ ነው ብለዋል።
የእስትሮክ የጤን እክል 25 በመቶ የሚያጠቃው ከሀያ እስከ ስልሳ አራት አመት ያሉ ሰዎችን መሆኑን የገለጹት ዶክተር ገላው እስፖርት፣ አመጋገብን ጨው ከበዛበት ምግብ መራቅ ፣ጮማና አልኮል እንዲሁም ስኳር መቀነስ ያስፈልጋል።
ሚዛንን አለመጠበቅ፣ የእይታ ችግር፣ ለመናገር መቸገር የፊት መጣመም ምልክቶች ከታዩ ስትሮክ ሊሆን ስለሚችል ወደ ሀኪም ፈጥኖ መሄድ ያስፈልጋል ብለዋል።
የእስትሮክ የጤና እክል በአለም ደረጃ 30 በመቶ የሚሆን ነዋሪ ተጋላጭ ሲሆን በሀገራችን ከ46 እስከ 51በመቶ ይደርሳል ያሉት ዶክተር ገላው የነርስ ባምላኩ መጽሐፍ ለማህበረሰቡ ግንዛቤ በመስጠት መከላከል እንዲችል አስተዋጽዎ አለው ብለዋል።

Address

Jimma
Jimma
NO

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Jimma University - Institute of health posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Jimma University - Institute of health:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram