Dr zuber Beyan, MD

Dr zuber Beyan, MD 𝓗𝓮𝓪𝓵𝓽𝓱 𝓫𝓵𝓸𝓰𝓼

19/07/2025

የልብ ደራሾቹ ጥንዶች

ክፍል አንድ

ዶክተር ኦብስኔት መርዕድ የዛሬ 13 ዓመታት ገደማ የህክምና ተማሪ እያለች ከአሜሪካን ተነስታ ወደኢትዮጵያ የመጣችው ለከፍተኛ ትምህርቷ የምርምር ሥራዎችን ለማከናወን ነበር። በወቅቱም ለምርምር ሥራዋ ምርጫዋ የነበረው ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ነው።

በሆስፒታሉ ያገኘችው የልብ ሃኪም የሆነው ዶክተር ስንታየሁ ወደኢመርጀንሲ ክፍል ወስዶ ከህክምና ትምህርት ቤት ተመርቆ በክፍሉ ተመድቦ ይሠራ ከነበረው የልብ ሃኪሙ ዶ/ር ተስፋዬ ጋር የምርምር ሥራዋን እንድታከናውን ያገናኛታል። ይሄ አጋጣሚ ነበር ዶ/ር ኦብስኔት መርዕድ እና ዶ/ር ተስፋዬ ተሊላን ያገናኛቸው። ባለሙያዎቹ እየተግባቡ፣ እየተላመዱም ቀጠሉ።

በሂደት ዶክተር ተስፋዬም ወደ አሜሪካ ተጓዘ። ለከፍተኛ ትምህርቱ ፈተናውን አልፎ የገባበት የህክምና ትምህርት ቤት ከዶ/ር ኦብሲኔት ጋር በቅርበት እንዲገናኙ አስቻላቸው። የከፍተኛ ትምህርታቸውንም አንድ ላይ ተማሩ። ሕይወት በአጋጣሚ ያገናኛቸው ሁለቱ ሃኪሞች በሙያ ከመተባበርም አልፈው በጋብቻ ተጣመሩ። ጥንዶቹ የአራት ልጆች አባትና እናት ለመሆንም በቁ።

አዳማ ተወልዶ ያደገው ዶክተር ተስፋዬ ተሊላ እንደሚናገረው፤ የህክምና ትምህርትን የተማረው ተወልዶ ባደገበት ኢትዮጵያ በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ህክምና ኮሌጅ ውስጥ ነው። ‹‹ከህክምና ኮሌጁ ትምህርቴን ያጠናቀቅኩት እአአ በ2008 ነው። ትምህርቴን እንደጨረስኩ ለአንድ ዓመት ከ10 ወራት በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ኢመርጀንሲ ክፍል ተቀጥሬ ሳገለግል ቆይቻለሁ›› ይላል።

የልብ ህክምና መማር ፍላጎት እንደነበረው የሚያስታውሰው ዶክተር ተስፋዬ፤ በዛን ጊዜ የልብ ህክምና ትምህርት በሀገር ውስጥ ባለመኖሩ በአሜሪካ ተምሮ ተመልሶ በሀገሩ ለመሥራት አቅዶ ቢጓዙም ከዶክተር ኦብስኔት ጋር የጀመሩት ግንኙነት ግን በአሜሪካ እንዲቆይ እንዳስገደደው ይናገራል። ለስምንት ዓመት በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ህክምና ኮሌጅ የተማረውን ትምህርት በማሳደግ በተጓዘበት ሀገረ አሜሪካ ለሰባት ዓመታት ያህል ተምሮ በልብ ህክምና ስፔሻላይዝድ ማድረግ መቻሉንም ነው የሚገልጸው።

ለስምንት ዓመታት በአትላንታ በሚገኝ ህክምና ተቋም በልብ ሃኪምነት እየሠራ የሚገኘው ትውልደ ኢትዮጵያዊው ሃኪም ዶክተር ተስፋዬ፤ ከዶክተር ኦብስኔት ጋር በጋብቻ ተጣምረን አራት ልጆች ወልደን እያሳለፍነው የምንገኘው በትዳርም በሙያችንም ስኬታማ የሆነ ኑሮ መሆኑንም ይናገራል። ‹‹ነገር ግን ስኬት ሲደረስባት ቶሎ ታረጃለች›› የሚለው ዶክተር ተስፋዬ፤ ስኬት ምንድነው ? የሚለው ጥያቄ ከባለቤቱ ዶክተር ኦብስኔት ጋር ሁሌም የሚያሰላስለው ሃሳብ መሆኑንም ይናገራል።

ዶክተር ኦብስኔት ከፍተኛ ህክምና ባለመኖሩ በህጻንነት እድሜዋ እህቷን አጥታለች፣ ዶክተር ተስፋዪ ደግሞ በቅርቡ አጎቱ በልብ ጉዳይ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል። አጎቱ የሞተ ቀን እሱ በአሜሪካ የ 92 ዓመት ዕድሜ ባለጸጋ ሴትዮ አክሞ አድኗል። ስለዚህ ‹‹እንዴትስ ተሳካልን እንላለን? ያሳደገን ሕዝብ መዳን በሚቻል ህመም እየረገፈ ተሳክቷል ማለት አይቻልም›› ሲል ይቆጫል።

ዶክተር ኦብስኔት አሜሪካን ሀገር ከፍላ ነው የተማረችው። ዶክተር ተስፋዬ ግን በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ህክምና ኮሌጅ ቁርስ፣ ምሳና እራት እየተመገበ ስምንት ዓመት የተማረው በነጻ ነው። በመሆኑም አገልግሎት መስጠት ውዴታ ሳይሆን ግዴታ መሆኑን ያስረዳል።

“አብልቶ፣ አጠጥቶ፣ አስተምሮ ለዚህ ክብር ያበቃኝን ጥቁር አንበሳ ሆስፒታልና ሕዝቤን በተራዬ ማገልገል አለብኝ›› ብሎ በበጎ ተግባር ላይ መሠማራቱንም ይናገራል። የኸርት አታክ ኢትዮጵያ ፋውንዴሽን ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶክተር ኦብስኔት መርድ ፋውንዴሽኑ የተመሠረተው በአሜሪካ ሀገር ይሁን እንጂ በኢትዮጵያም የተመዘገበ ድርጅት ነው ትላለች።

ኸርት አታክ ኢትዮጵያ (Heart attack Ethiopia) የበጎ አድራጎት ድርጀት አቅም ላጡ የልብ ሕሙማን እያገዘ ይገኛል። ኑሯቸውን በአሜሪካ ያደረጉት እነዚህ ጥንዶች ከተለያዩ በጎ አድራጊዎች ባሰባሰቡት ገንዘብ ከተለያዩ ሀገራት የተውጣጡ 33 የሕክምና ባለሙያዎችን አስተባብረው ወደ ኢትዮጵያ በማምጣት ለአራተኛ ጊዜ በሶስት ማዕከላት የልብ ቀዶ ህክምና እየሰጡ ናቸው።

ዶክተር ተስፋዬ እንደሚገልፀው ብዙ ላይሆን ቢችልም የአንድ ሰው ሕይወት ማገዝም አስፈላጊ ነው። የበጎ አድራጎቱ መሠረቱም ይሄ ነው። ገንዘብ ተርፏቸው ወይም ዝነኛ ለመሆን አሊያም ሌላ ምክንያት አንግበው አይደለም ወደ ኢትዮጵያ የመጡት። እንደእርሱ ማብራሪያ፤ በመጀመሪያ ተግባሩ በትንሹ ይጀመር በሚል ሃሳብ ስድስት ባለሙያዎችን ይዘው መጥተው ለ32 ሰዎች ነበር የሠሩት። ሆኖም የነገሩ አስፈላጊነት ሥራውን እንዲያድግ አደረገ። ትግበራው ግን በቋፍ የቆመ ነገር እንደነበር ለመገንዘብ አስችሏል።

ይሄ ሁሉ አገልግሎት ፈላጊ እያለ ቢያድግ ጥሩ ነው የሚል ግፊት ነበር፣ እነሱም የበለጠ ለመሥራት ተነሳሱ። አክመውና ፈውስ ሰጥተው በሚሄዱት ሳይሆን አገልግሎቱን ባላገኙት ያዝናሉ። ለዚህም ነው ወደ ኢትዮጵያ መመላለስ ያዘወተሩት። 33 ባለሙያዎች ይዘው በመምጣት ከ32 ታካሚ በመነሳት በዚህ ዙር እስካለፈው ረቡዕ ማለዳ ድረስ 135ኛ ታካሚዎችን ልብ ፈውሰዋል።

ይህንን ዙር ሲያጠናቅቁ 150 ሰው ቀዶ ህክምና ሊሰራለት ይችላል ብለው ያስባሉ። ትልቅ ችግር መሆኑን ተገንዝበዋል። በመሆኑም ቆርጠው ተነስተዋል። ነገር ግን ብቻቸውን የሚጨርሱት እንዳልሆነ ያምናሉ። የህክምናው ወጪና ድጋፍ የኸርት አታክ ኢትዮጵያ ፋውንዴሽን ሥራው ሲጀመር በሁለታቸው አቅም ነበር። ይሄንን ያህል ታካሚ ለማከም እንችላለን በሚል አልነበረም የጀመሩት። ነገር ግን በአሜሪካ መኖራቸው ለትግበራው ጥቅም ማስገኘቱን የፋውንዴሽኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶክተር ኦብስኔት ሀብት በማሰባሰብ ህክምና የሚያስፈልጋቸውን ኢትዮጵያውያንን መደገፍ አለብን በሚል በመጀመራቸው ብዙ ጊዜ አስፈላጊ ቁሳቁሶችንና መድሃኒቶችን በርዳታ እያገኙ መሆኑንም ትናገራለች።

ዶክተር ኦብስኔት እንደምትናገረው ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ መተዳደሪያ ሥራቸውን አቁመው ነው። ነገር ግን ብዙ ወጪዎች የሚሸፈኑት አሜሪካ በሚገኙ የተለያዩ ኩባንያዎች ነው። ግለሰቦችም ድጋፍ ያደርጋሉ። አሁን የገንዘብ ማሰባሰብ እንቅስቃሴ እያደረጉ ይገኛሉ። በመጀመሪያ ዙር ሲመጡ ይዘው የመጡት 350 ሺህ ዶላር የሚፈጅ ቁሳቁስ ነበር።

አገልግሎቱን የሰጡት በአንድ ቦታ በልብ ማዕከል ብቻ ነበር። አሁን አገልግሎት መስጫ ቦታን ወደ ሶስት ቦታ አሳድገዋል። በጥቁር አንበሳ ስፔሻይዝድ ሆስፒታል፣ በልብ ህሙማን ማዕከል እና በቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል እየሠሩ ይገኛሉ። መስፋፋታቸው ደግሞ አስፈላጊ ቁሳቁሶች እንዲጨምር ያደርጋል የሚሉት ዶክተር ኦብስኔት፤ በዚህ የልብ ደራሾቹ ጥንዶች ዙር ይዘው የመጡት ቁሳቁስ ሁለት ሚሊዮን ዶላር ዋጋ የሚያወጣ ነው። ብዙ ርዳታ ያገኙትም ሥራቸው ከታየ በኋላ ነው።
እንደ ዶክተር ተስፋዬ ገለፃ በዚህ ጉዳይ ብዙ ገንዘብ ያወጣሉ፤ ይሁን እንጂ በተግባሩ ደስታቸው እጥፍ ድርብ ሆኗል። ለተግባሩ ኩባንያዎች እገዛቸው ትልቅ እየሆነ ነው። ሥራውን ውድ የሚያደርገው የሚሠሩበት እቃ ዋጋው ውድ በመሆኑ ነው።

ባለሙያዎችንም ማጓጓዝ በራሱ በጣም ውድ ነው። እንደገና ደግሞ 125 የሚደርሱ ሻንጣዎችን ይዘው ነው የመጡት። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከመጀመያው ዙር ጀምሮ ተግባሩን ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በሚኖራቸው ጉዞ ወቅት እያገዘ ይገኛል። የነጻ ትኬት እና የቅናሽ ትኬት ተጠቃሚ አድርገዋቸዋል። የሚጓጓዙ ጭነቶችም በነጻ እንዲጓጓዝ በማድረግ ለትግበራው ስኬት ተባባሪ ሆኗል።

የጤና ሚኒስቴር የችግሩን ግዝፈት በመገንዘብ ሥራው እንዲሳለጥና ታካሚዎች አገልግሎቱን እንዲያገኙ በማድረግ በኩልም እገዛ አድርጓል። ችግሩ ብዙ ቤተሰብ ላይ ተጽእኖ በማሳረፍ እየጎዳ መሆኑ ታውቋል። በመጀመሪያ ዙር የመጡ ጊዜ የልብ ጉዳይ ያን ያህል ችግር ነወይ የሚሉ ነገሮች ይነሱ ነበር። አሁን በሚታይ ሁኔታ ሆኗል።

በህክምናው ሰዎች ታክመው እየዳኑ ናቸው። የዳኑት ራሳቸው ምስክርነት እየሰጡ ይገኛሉ። አሁን የቀረበው አገልግሎት በቂ ነው የምንልበት ደረጃ ላይ አይደለንም ይላሉ። ጅማሮው ጥሩ ሆኖ ተገኝቷል። አገልግሎቱ በርዳታ ደረጃ በመሆኑ እንጂ በዋጋ ቢተመን ውድ ነው። ለማስቀጠል የሚቻልበትን ሁኔታ እየሞከሩ መሆኑን ዶክተር ተስፋዬ ያስረዳል።
በቀጣይ ሳምንት አምዳችን የኸርት አታክ ኢትዮጵያ (Heart attack Ethiopia) በአራተኛ ዙር ህክምና የተሰጣቸው ታካሚዎች ሁኔታ፣ በትግበራው የገጠማቸውን ስኬትና ተግዳሮት በተመለከተ ይዘን እንቀርባለን ።

08/06/2025

Ethiopia Launches Roadmap to Reduce Teenage Pregnancy: A National Call for Action
On June 5, 2025, Ethiopia took a monumental step toward safeguarding the health and future of its adolescents with the official launch of the Teenage Pregnancy Reduction Roadmap 2025–2030. The high-level event, held at Hyatt Regency, brought together key stakeholders, including representatives from the Ministry of Health, Ministry of Women and Social Affairs, Ministry of Education, and Ministry of Planning and Development, along with development partners and civil society organizations.
The event served as both the official launch of the roadmap and a signing ceremony for the Memorandum of Understanding (MOU) among the collaborating ministries. The roadmap outlines a multi-sectoral approach to addressing the country’s high rates of teenage pregnancy, one of the leading causes of morbidity and mortality among adolescents in Ethiopia.
The program featured presentations highlighting the severity of adolescent health challenges, with a focus on the critical role of teenage pregnancy in impeding educational opportunities and exposing young girls to significant health risks. Stakeholders discussed root causes, including social, economic, and cultural drivers, and identified strategic interventions aimed at prevention, protection, and empowerment.
Participants pledged their commitment to cross-sectoral collaboration, community engagement, and evidence-based action to drive down adolescent pregnancy rates. Among the key priorities were comprehensive sexuality education, youth-friendly reproductive health services, and strengthening policies that protect the rights of adolescents—particularly girls.
The Ethiopian Society of Obstetricians and Gynecologists (ESOG), as a key stakeholder in adolescent and reproductive health, stands committed to supporting the implementation of this strategic plan through clinical, research, and advocacy efforts and recommends localization of the efforts to end teenage pregnancy. We join our partners in celebrating this vital milestone and reaffirm our dedication to ensuring that every Ethiopian adolescent has the opportunity to grow, thrive, and lead a healthy, empowered life.
Together, we can end teenage pregnancy and build a healthier future for Ethiopia’s youth.

From Rome (Italy ) to Beijing (China)🌍 Yaala Ammayyaa Keessatti Isa Jalqabaa Seena-qabeessa! 🚑🤖Agarsiisa kalaqaa dinqisi...
08/06/2025

From Rome (Italy ) to Beijing (China)
🌍 Yaala Ammayyaa Keessatti Isa Jalqabaa Seena-qabeessa! 🚑🤖

Agarsiisa kalaqaa dinqisiisaa ta'een, baqaqsartuun Chaayinaa tokko milkaa'inaan baqaqsanii hodhuu fageenyaa ardiiwwan gidduu kan addunyaa irratti isa jalqabaa raawwateera — dhukkubsataa Beejiing jiru irratti hojii baqaqsanii hodhuu gaggeessaa, ofii isaanii qaamaan Roomitti argamaa turan! 🌐✋

Sirna baqaqsanii hodhuu roobootii teeknooloojii cimee qabuufi neetworkii qunnamtii 5G saffisa olaanaa qabu fayyadamuun, baqaqsartuun meeshaalee baqaqsanii hodhuu sirrummaa dinqisiisaa ta'een too'achuu danda'eera, kiiloo meetira kumaatamaan lakkaa’amu fagaatanii ta’anis. 🛰️

✨ Kun maaliif jijjiirama guddaa fida?

✅ Baqaqsanii hodhuu addaatiif gufuulee joograafii ni dhabamsiisa.
✅ Dhukkubsattoota naannoo fagoo yookiin tajaajila gahaa hin qabneef kunuunsa ogeessaa ga'uu danda'a.
✅ Walta’iinsa fayyaa addunyaa dhugaa ta’eef karaa saaqa.
✅ Dhukkubsattoota gargaarsa ogeessaa sadarkaa addunyaa barbaadaniif yeroofi baasii ni hir’isa.

🌟 Cabsii guddaan kun humna roobootiksii, dabarsuu odeeffannoo battalumatti (real-time), fi leenjii yaalaa sadarkaa olaanaa walitti qaba – kunis gara fuulduraa tajaajila fayyaa as jiraachuu isaa mirkaneessa. 🚀

👉 Addunyaa fageenyi argama gargaarsa ogeessaa fayyaa lubbuu baraaruu hin daangessine yaaduu dandeessuu? Carraawwan jiran daangaa hin qaban.

09/04/2025

With Zuber Beyan – I'm on a streak! I've been a top fan for 8 months in a row. 🎉

14/03/2025
Pneumonia is the single largest infectious cause of death in children. It's a form of acute respiratory infection affect...
26/02/2025

Pneumonia is the single largest infectious cause of death in children. It's a form of acute respiratory infection affecting the lungs 🫁 that is caused by viruses, bacteria, or fungi. The good news is that it can be prevented - here's how ⬇️
WWorld Health Organization (WHO)

17/02/2025

Ofiin Ba'uu Ulfaa (Miscarriage, Spontaneous Abortion).

Ofiin ba'uu ulfaa (Spontaneous Abortion) jechuun yoo ulfi tokko ofuma isaan ba'u jechuudha. Dhibeen kun dubartoota garratti hafe (ulfaa'an) keessaa 15% (ulfa afur keessaa tokko) kan mudatudha. Ba'uun ulfaa kun dubartii tokko yoo al lamaa fi isaa ol mudate "Ofiin ba'uu ulfaa irraa deddeebi'aa" ykn Recurrent Miscarriage jedhama. Yeroo kanatti mana yaalaa deemtee of qorachiisuun dirqama ta'a.

MAALTU FIDAA?
1. Ofiin ba'uu ulfaa keessaa dhibbeentaan 50 (50%) kan ta'u yoo micireen uumamtu, lakkoofsi kiroomosomii doggoggoramuu irraa kan ka'e dha.

2. Dhibeewwan gadameessaa akka:
- Dhibee gadameessaa kan uumamaa, kan akka "Septate Uterus" ykn yoo gadameessi tokko ta'uu male, uumamaan balla lamatti hiramee dhalatu.
- Yoo dhaabni gadameessaa sababa walitti qabatee (maxxanee) micireef bakki ga'aan dhabamu (Asherman Syndrome).
- Dhiitaa "ixii" gadameessa keesaatti uumamu (Uterine myoma, polyps)
- Sirnaan cufachuu dadhabuu ulaa gadameessaa (Cervical insufficiency)

3. Dhibee qaamaa (kan gadameessaa alaa) ofiin ba'uu ulfaaf saaxilan:
- Dhukkuba sirna maadinummaa kan antiphospholipid syndrome jedhamu.
- Dhukkuba sukkaaraa
- Dhibee xannacha taayirooyidii
- Dhibee oovaarii kan polycystic o***y syndrome jedhamu.

YAALA
Yaalli dhibee ofiin ba'uu ulfaa kun kan kennamu ogeessota Speeshaalistii ulfaa fi gadameessaan yoo ta'u, ka'umsa isaa adda baasuuf qorannoon ga'aan erga godhamee booda, ka'umsa isaa irratti hundaa’uun yaalli kennama.

Dr. Lemi Belay (Speeshaalistii Ulfaa fi Gadameessaa , Subspeeshaalistii Fayyaa Wal hormaataa)

08/12/2024

Have a blessed weekend!!!

07/12/2024

African vs white ?

የማህጸን በር ካንሰር በሽታ በአለም እንዲሁም በሀገራችን ከጡት ካንሰር ቀጥሎ ለበርካታ ሴቶች ህመም እና ሞት ምክንያት ከሆኑት በሽታዎች አንዱ ነው፡፡ ይህ በሽታ በሀገራችን በየአመቱ ከ 8,1...
19/11/2024

የማህጸን በር ካንሰር በሽታ በአለም እንዲሁም በሀገራችን ከጡት ካንሰር ቀጥሎ ለበርካታ ሴቶች ህመም እና ሞት ምክንያት ከሆኑት በሽታዎች አንዱ ነው፡፡

ይህ በሽታ በሀገራችን በየአመቱ ከ 8,168 በላይ የሚሆኑ ሴቶችን የሚያጠቃ ሲሆን የጤና ሚኒስቴር ከ9-14 አመት ላይ ያሉ ወደ 7 ሚሊዮን የሚሆኑ ሴት ህፃናትን ለመከተብ ዝግጅታችንን ጨርሰናል።

የማህፀን በር ካንሰርን የማጥፋት ቀንን ስናከብር ይህንን በቀላሉ መከላከል የምንችለውን በሽታ ለማጥፋት የገባነውን ቃልኪዳን በማስታወስ የሴቶችን ጤና ለመጠበቅ በርትተን የምንሰራ ይሆናል።

Cervical cancer remains the fourth most common cancer worldwide, impacting over 8,168 women here in 🇪🇹.

On this , we reaffirm our dedication and renew our commitment to eliminating this preventable disease.

Ministry of Health,Ethiopia has pledged to provide vaccines to 7 million children with the age range of 9-14 years.

Together, let us strengthen our efforts to protect the health and future of women everywhere.

Address

J83G+28P
Mechara
J83G+28P

Telephone

+251913202957

Website

https://m.me/Drzubermediumclinic, https://drzuber.com.et/, https://t.me/Drzubermedium

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dr zuber Beyan, MD posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram