Wolaita Sodo University School of Public Health Office

Wolaita Sodo University School of Public Health Office School of Public Health @ ottona Comprehensive & specialized Hospital

 መልዕክቱ ለሚመለከተው አካል እንዲደርስ ሼር በማድረግ ተባበሯቸው'' ስለ ወላይታ ሶዶ ጤና ተማሪዎች ጠይቁልን እድሜ እየገበርን ነው  በመመረቂያ ሰዓታችን ገና ከአንድ ዓመት በላይ የሚያቆይ ...
14/09/2024


መልዕክቱ ለሚመለከተው አካል እንዲደርስ ሼር በማድረግ ተባበሯቸው

'' ስለ ወላይታ ሶዶ ጤና ተማሪዎች ጠይቁልን እድሜ እየገበርን ነው በመመረቂያ ሰዓታችን ገና ከአንድ ዓመት በላይ የሚያቆይ የትምህርት ጊዜ ቆይታ አለብን እንዲም ሆኖ በየ ሰበቡ እያስወጣ ለሚያቆየን + ኋላ ቀርተን ሳለ የሌላው ዩኒቨርሲቲ የጤና ግቢ ተማሪ በሚማርበት ሰዓት እኛ ለ3ት ወር ቤት ለተዘፈዘፍነው + የኣዕምሮ ጭንቀት ውስጥ ላለነው + ከጓደኞቻችን /ከባቻችን ከአንድ ዓመት በላይ ወደኋላ ቀርተን ላለነው + ገብተንም እንዴትናቹ
ለማንባለው እንደ በሶ በተበጠበጠ ሽሮ ለምንኖረው + ኣመት ላመት በበጀት ኣለቀ እየተሳቀቅን ላለነው + በዚህ ሰዓት ሁላችንም ከጓደኛ ተለይተን ብቻችን ለቀረነው + ለቤተሰቦቻችን መች ትመረቃላቹ ጥያቄ ዛሬ ከ4ት ዓመት በኋላ መልስ ለሌለን ለእኛ ለወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኦቶና ካምፓስ ጤና ሳይንስ ተማሪዎች ድምፅ ሁኑን ድረሱልን ከባድ ምሬት ውስጥ ነን ክብድ ብሎናል እባካቹ ጠይቁል.......😢😢😢😭😭😭😭😭

👇👇👇👇👇👇👇👇👇

እኛ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኦቶና ካምፓስ ጤና ሳይንስ ተማሪዎች በኮቪድ-19 ወረርሽኝና በተለያዩ ሀገራዊ ችግሮች ምክንያት ሲባክንብን የነበረው የትምህርት ክፍለ ጊዜ ሊያካክስልን ሲገባ ግቢው በግድየለሽነት አዘግይቶ እየጠራንና አስቀድሞ ከግቢ እንድንወጣ በማድረግ መመረቅ ካለብን ጊዜ ከአንድ ዓመት በላይ እንዲባክንብን ወይም ወደኋላ እንድንቀር አድርጎናል።

👇👇👇👇👇👇👇👇

አሁን ላይ ያለንበት ሁኔታ በዝርዝር ለመመልከት ያክል

የ2012 ባች የpharmacy ዲፓርትመንት ተማሪዎች ዘንድሮ 2016 ዓ.ም መመረቅ ሲገባን ገና 5ኛ ዓመትን አልጀመርንም

የ2013 ባች በ4 ዓመት የምረቃ ፕሮግራም መሰረት ዘንድሮ 2016 ዓ.ም መመረቅ የነበረብን የሁሉም ዲፓርትመንት የጤና ተማሪዎች ገና 3ኛ ዓመትን አልጨረስንም

የ2014 ባች አጠቃላይ የሁሉም ዲፓርትመንት ጤና ተማሪዎች ዘንድሮ 3ኛ ዓመትን ማጠናቀቅ ሲኖርብን ገና አልጀመርንም

የ2012 ባች የMedicine ዲፓርትመንት ተማሪዎች ዘንድሮ 5ኛ ዓመትን ማጠናቀቅ ሲኖርብን ገና አልጀመርንም

የ2013 ባች የpharmacy እና Medicine ዲፓርትመንት ተማሪዎች ዘንድሮ 4ኛ ዓመትን ማጠናቀቅ ሲኖርብን ገና 3ኛ ዓመትን አልጨረስንም

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

ስለሆነም ከሌላው ዩኒቨርሲቲ አቻ ባቾቻችን ጋር በተመሳሳይ ጊዜ ተመርቀን እንደ ሀገር እኩል ተወዳድረን የስራ እድል ማግኘት የምንችልበትንና ወደፊት የሞያ እድገት ደረጃችን ማሻሻል የምንችልበትን ጊዜ በከንቱ መባከኑን ተከትሎ እየደረሰብን ያለው የስነ ልቦና ጫና እና እያመለጠን ያለው የስራ እድል እንዲሁም እስካሁን አስተምረው የእኛን ወግ ማዕረግ ለማየት በጉጉት እየጠበቁ የሚገኙት ቤተሰቦቻችን የእኛ ከምረቃ መዘግየት እያሳደረባቸው ያለውን የሞራል ውድቀት እና የኢኮኖሚ ብክነት ከግምት በማስገባት የሚመለከተው አካል ተገቢውንና ፈጣን የመፍትሔ ምላሽ እንዲሰጠን ስንል በታላቅ ትህትና እንጠይቃለን። ''

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኦቶና ካምፓስ ጤና ሳይንስ ተማሪዎች

ለበለጠ መረጃ በTelegram group and channel ቤተሰብ ይሁኑ

t.me/HSM077
t.me/WsuHealthOfficers

ሁሉም የጤና ሳይንስ ተማሪ join ማድረግ የሚገባው ምርጥ ግሩፕ ይሄንን ሊንክ በመጫን join አድርጉ👇👇👇👇
14/09/2024

ሁሉም የጤና ሳይንስ ተማሪ join ማድረግ የሚገባው ምርጥ ግሩፕ
ይሄንን ሊንክ በመጫን join አድርጉ
👇👇👇👇

በየወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ተማሪዎች ከ2013 ባች ጀምሮ ያለን የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኦቶና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ተማሪዎች ከገባንበት ቀን ጀምሮ በተለያዩ ምክንያቶች ከም...
30/08/2024

በየወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ተማሪዎች

ከ2013 ባች ጀምሮ ያለን የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኦቶና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ተማሪዎች ከገባንበት ቀን ጀምሮ በተለያዩ ምክንያቶች ከምንመረቅበት አመት በጣም ወደ ኋላ እየቀረን ነው ድምፃችን አሰሙልን ሲሉ ቅሬታ አድርሰውናል።

📌 የ2012 ባች pharmacy ተማሪዎች አሁንም ገና 5th yr እየጀመሩ ነው።(መጨረስ የነበረባቸው)

📌የ2013 ባች ተማሪዎች እስካሁን ማለትም ነሐሴ 22/2016ዓ.ም ድረስ የ3rd year ትምህርት አላጠናቀቁም።(አራተኛ ዓመት መጨረስ የነበረባቸው)

📌 የ2014 ባች ተማሪዎች ደግሞ በቀደሙ ባቾች መዘግየት ምክንያት ብዙ መማር እየቻሉ አሁን ገና 3rd yr ሊገቡ ነው።(የሶስተኛ ዓመት ትምህርት መጨረስ የነበረባቸው)

እኛ በባቻችን የመመረቅ እና ከኛ ባቾች ጋር ተወዳድረን የመስራት መብት አለን ያሉት ተማሪዎቹ ቤተሰቦቻችን በተለያዩ ችግሮች ውስጥ ሆነው ከሌላቸው እየቀነሱ አስተምረው ቶሎ እንድንደርስላቸው ቢመኙም ዩንቨርሲቲው በዕድሜያችን ላይ እየቀለደ ነው ሲሉ ቅሬታቸውን ገልፀዋል።

የበጀት እጥረት የሁልጊዜ ምክንያት ሆኖ በተለያዩ ጊዜያት ከግቢ እንድንወጣ እያደረጉ ለብዙ ወጪ እና እንግልት ዳርገውናል።መቼ እንደምንመረቅ አናውቅም።ይህን ቅሬታችንን የሚመለከተው አካል ሰምቶ #አፋጣኝ መፍትሄ ይስጠን ሲሉ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ተማሪዎች ጠይቀዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

t.me/WsuHealthOfficers
t.me/WsuHealthOfficers
t.me/WsuHealthOfficers

የክረምት የጤና በጎ አድራጎት ስራዎች  ዛሬም ተጠናክሮ ቀጥሏል ። ***********************************የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ  ጤና ሳይንስና   ሕክምና ኮሌጅ ኮምፕርሄን...
17/08/2024

የክረምት የጤና በጎ አድራጎት ስራዎች ዛሬም ተጠናክሮ ቀጥሏል ።
***********************************
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ኮምፕርሄንሽቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የ2016 ዓ.ም ''በጎነት ለጤናችን ''በሚል የክረምት የጤና በጎ ፍቃድ አገልግሎት በተለያዩ የጤና ምርመራ ፣ሕክምና እንዲሁም በጤና ትምህርት አጠናክሮ ቀጥሎ ውለዋል።
ለጤናዎ ይገደናል፣
ዕውቀትን በተግባር!
የኮሌጁ ኮሙኒኬሽንና ሕዝብ ግንኙነት
ሐምሌ 2016ዓ.ም

👉 ከሐምሌ እስከ ጳጉሜ

ትምህርት ሚንስተር ለሁሉም ዩኒቨርሲቲ  ወጥ የሆነ ፕሮግራም ማውጣቱ ጥሩ ሆኖ ሳለ : የጤና ተማሪዎችን በተለይም በተለያዩ ሀገራዊ ችግሮች ምክንያት 1 እና 2 ዓመት ሙሉ ወደኋላ የቀሩ ባቾችን...
17/08/2024

ትምህርት ሚንስተር ለሁሉም ዩኒቨርሲቲ ወጥ የሆነ ፕሮግራም ማውጣቱ ጥሩ ሆኖ ሳለ : የጤና ተማሪዎችን በተለይም በተለያዩ ሀገራዊ ችግሮች ምክንያት 1 እና 2 ዓመት ሙሉ ወደኋላ የቀሩ ባቾችን መሰረት ያደረገ ባለመሆኑ ት/ት ሚኒስትር አጠቃላይ በ year based curriculum መሰረት ለሚማሩ ተማሪዎች እና ሳይካካስላቸው 1 እና 2 ዓመት ሙሉ ወደኋላ የቀሩ ተማሪዎችን ያማከለ የተለየ ፕሮግራም ካልቀረፀ በስተቀር አሁን የወጣው ፕሮግራም የተማሪዎችን ጊዜ ከመግደል ባለፈ ሌላ ጥቅም ሊኖረው አይችልም።

ከስር ያለውን ሊንክ በመጫን የቴሌግራም ቻናላችን ቤተሰብ ይሁኑ
👇👇👇👇👇👇👇
t.me/WsuHealthOfficers
t.me/WsuHealthOfficers
t.me/WsuHealthOfficers

ይህ ቻናል ከወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ህብረተሰብ ጤና ሳይንስና ህክምና ትምህርት ቤት ጋር ተያያዥነት ያላቸው መረጃዎችንና ከዚህ በፊት ተመርቀው ስራ ላይ የሚገኙ የቀድሞ የዲፓርትመንቱ ተማሪዎች...
17/08/2024

ይህ ቻናል ከወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ህብረተሰብ ጤና ሳይንስና ህክምና ትምህርት ቤት ጋር ተያያዥነት ያላቸው መረጃዎችንና ከዚህ በፊት ተመርቀው ስራ ላይ የሚገኙ የቀድሞ የዲፓርትመንቱ ተማሪዎች ልምዳቸውን የሚያካፍሉበት ቻናል ሲሆን ከስር ያለውን ሊንክ በመጫን የቻናሉ ቤተሰብ እንድትሆኑ ስንል ጋብዘናችኋል!

መልዕክቱ ለሁሉም ተደራሽ እንዲሆን ወደእየ Telegram ግሩፓቹ ሼር በማድረግ እንድትተባበሩን ስንል በትህትና እንጠይቃለን👏👏👏

ሊንኩ
👇👇👇👇👇

t.me/WsuHealthOfficers

 's  ▭▭▭▭▭▭▭▭▭▭▭ቁጥራቸው ወደ 800 የሚጠጉ የኦቶና ሆስፒታል ጤና ባለሙያዎች አስተዳደራዊ በደል ደርሶብናል በሚል ቅረታቸውን በፊርማቸው በማረጋገጥ ለወሶዩ ፕረዚዳንት አሰሙ!=====...
08/08/2024

's
▭▭▭▭▭▭▭▭▭▭▭
ቁጥራቸው ወደ 800 የሚጠጉ የኦቶና ሆስፒታል ጤና ባለሙያዎች አስተዳደራዊ በደል ደርሶብናል በሚል ቅረታቸውን በፊርማቸው በማረጋገጥ ለወሶዩ ፕረዚዳንት አሰሙ!
==================================
የወሶዩ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ኦቶና ሆስፒታል ክሊኒካል ጤና ባለሙያዎች ቅሬታቸውን ለዩኒቨርስቲው ፕረዚዳንት አሰሙ!
===================================
በወሶዩ የጤና ሳይንስ እና ሕክምና ኮሌጅ ክሊኒካል ሰራተኞች የኮሌጁ የበላይ አመራር አካላት በሶስት ዋና ዋና ሐላፊዎች/ዳይሬክተሮች በቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ፣ቺፍ ክሊኒካል እና ቺፍ አካዳሚክና ምርምር ዳይሬክተሮች የተፈፀሙ አስተዳደራዊ በደል የሐላፊነት ጊዜ ያለፈባቸውን በጥቅም ተጋሪነት ጎጤኝነት ጓደኝነት ያለ ውድድር ሆን ተብሎ የፈለገውን በፈለገው መደብ ያለመደባቸው ብቃት የሌላቸውን ከሲቪል ሴርቭስ አሰራር ውጪ ከሓላፊነት እስከ ሥልጠና የተለያዩ ጥገኛ አሰራር እንዲሁም ሌሎች የሚገባቸውን መመሪያ የፈቀዳላቸውን በአዋጅ የፀደቀውን የፌዴራል መንግስት ሰራተኞች አዋጅ 2012 ዓ/ም መሰረት የተፈቀደላቸውን ኬረሪ የደመወዝ እርከን ማሻሻያ የተከለከላቸው ወደ ስምንት መቶ ክሊኒካል ሰራተኞች እና አካዳሚክ ሰራተኞች በተለያዩ ምድብ ለዩኒቨርስቲው ፕረዚዳንት ከፕሬዝዳንቱ ጋራ በቂ ምክክር እና ውይይት በፕሬዝዳንት ቢሮ በአካል ከአራት ሴርቭስ መኪና በላይ ምሽት 2:00 ድረስ በከፍተኛ ምሬት እና እሮሮ መንግስት በአዋጅ እና መመሪያ ያስተላለፈውን ጥቅማጥቅም በቢልሹ አሰራር ተከልክለው በአንፃሩም የማይገባቸው በርካታ መደቦች ከመደብ ውጪ የተመደቡ እንዲሁም በሓላፊነት ተርማቸው አልፈውም ሆን ተብሎ በነዚህ ሶስት የአንድ አከባቢ እና ሰፈር የበላይ አመራሮች የተፈፀመውን አቅርበው ፕረዚዳንቱ ለሚመለከተው የአስተዳደር ፍ/ቤት ተጠሪነቱ ለሲቪል ሴርቭስ የሆነው የአስተዳደር ዳኝነት ተቋማዊ ፍትህ የውሳኔ ሀሳብ እንዲያቀርብ የመራው ሲሆን ውሳኔውን አስተዳደራዊ ዳኝነት ላይ አስተዳደራዊና ሕጋዊ በተለይም ከመደብ ውጪ ሰራተኞችን መመደብ ማንኛውም ሐላፊ በሕግ የሚያስጠይቅ በመሆኑ ሕጋዊ እርምጃ ለመውሰድ ማኔጅመንቱ ውሳኔ እየተጠበቀ መሆኑን ለመረዳት ተችሏል !

የጤና ባለሙያዎቹ አካላዊ ጥቃት ጭምር በሐላፊዎቹ ትዕዛዝ ይደርስብናል በሚል ለወሶዩ ፕረዚዳንት በርካታ ቁጥር ያላቸው በአካል ጭምር ተገኝተው በምሬት ቅሬታቸውን አቅርበዋል !

በመሬት መንሸራተት አደጋ ምክንያት ህይወታቸው ላጡ የጋሞ ጎፋ ወገኖቻችን ነብሳቸው በአፀደ ገነት ያኑርልን 🙏🙏🙏
23/07/2024

በመሬት መንሸራተት አደጋ ምክንያት ህይወታቸው ላጡ የጋሞ ጎፋ ወገኖቻችን ነብሳቸው በአፀደ ገነት ያኑርልን 🙏🙏🙏

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የ2013 ዓ.ም ባች  ጤና ሳይንስና ህክምና ኮሌጅ የሚማሩ 2016 ዓ.ም መመረቅ ሲገባቸው ተጨባጭነት በሌለው ምክንያት ሳይመረቁ የቀሩት ሁሉም የጤና ተማሪዎች መጪው ...
22/07/2024

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የ2013 ዓ.ም ባች ጤና ሳይንስና ህክምና ኮሌጅ የሚማሩ 2016 ዓ.ም መመረቅ ሲገባቸው ተጨባጭነት በሌለው ምክንያት ሳይመረቁ የቀሩት ሁሉም የጤና ተማሪዎች መጪው ዓመት 2017 ይመረቁ የምትሉ ሼር ላይክ እና ኮሜንት አድርጉ 🥺🥺🥺

ለሚመለከተው ሁሉየ2013 ዓ.ም ባች የወላይታ ሶዶ ኦቶና ጤና ሳይንስና ህክምና ኮሌጅ የጤና መኮንን ( public heath ) ተማሪዎች ጋወን እና stethoscope ከሌላ ዲፓርትመንት ተውሰ...
28/06/2024

ለሚመለከተው ሁሉ
የ2013 ዓ.ም ባች የወላይታ ሶዶ ኦቶና ጤና ሳይንስና ህክምና ኮሌጅ የጤና መኮንን ( public heath ) ተማሪዎች ጋወን እና stethoscope ከሌላ ዲፓርትመንት ተውሰው ward መጀመራቸው ሳያንስ : ከመመረቂያ ጊዜ አንድ ዓመት ከምናምን ወደኋላ መቅረታቸው ያማረራቸውና ተስፋ ያስቆረጣቸው የዲፓርትመንቱ ተማሪዎች ጋወን እና stethoscope ተሟልቶ የመመረቂያ ፕሮግራሙ ወደ 2017 እንዲደረግላቸው በምሬት ተናገሩ ተማሪዎቹ አክለውም እድሜያችን በከንቱ በማባከኑና ከሌሎች ግቢ አንፃር አንድ አመት ከምናምን ወደኋላ መቅረታችን ያስከተለብንን የሞራል ውድቀት የሁለት ዓመት የሞራል ካሳ ሊሰጠን ይገባል ሲሉ ተደምጠዋል።

ፔጃችን follow እና like ያድርጉ መልዕክቱን ለሌሎች share በማድረግ ድምፅ እንሁን✔️

በዩኒቨርሲቲው ከህብረተሰብ ጤና ትምህርት ቤት ተማሪዎች የመማርና ማስተማር ሂደት ጋር ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮችን እያነሳን መወያየት እንዲያስችለን እንዲሁም ከዚሁ ግቢ ተመርቀው በተለያዩ የሀ...
30/03/2024

በዩኒቨርሲቲው ከህብረተሰብ ጤና ትምህርት ቤት ተማሪዎች የመማርና ማስተማር ሂደት ጋር ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮችን እያነሳን መወያየት እንዲያስችለን እንዲሁም ከዚሁ ግቢ ተመርቀው በተለያዩ የሀገሪቷ ክፍል ተቀጥረው ስራ ላይ የሚገኙ የቀድሞ ተማሪዎች ልምዳቸው የሚያካፍሉበት ትልቅ የመገናኛ ብዙሃን ይሆን ዘንድ መልዕክቱ ብዙዎች ጋር እንዲደርስ ሼር በማድረግና ሌሎች follow እንዲያደርጉ በመጋበዝ ቤተሰባዊ አላፊነታችን እንወጣ እንላለን!
መልካም ቆይታ🖐
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሰቲ የህብረተሰብ ጤና ተማሪዎች ድምፅ✅

Address

Wolaita Sodo
Sodo

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wolaita Sodo University School of Public Health Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram

Category