WSU College of Health Science and Medicine - ወሶዩ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ

  • Home
  • Ethiopia
  • Sodo
  • WSU College of Health Science and Medicine - ወሶዩ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ

WSU College of Health Science and Medicine - ወሶዩ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ Former, the college was called “Otona Hospital” established in 1928 as Small Clinic ; now WSU,CHSM

Wolaita Sodo University College of health science and medicine was established in 1928 as small clinic by Dr Thomas Lambe , missionary. Served for 50 years as primary hospital and for 30 years as general hospital. The hospital amalgamated with Wolaita Sodo University in 2004 E.C with academic responsibility ,demand driven research ,community service and quality clinical services . VISION

The college aspires to be one of the top five colleges of Health Science and Medicine in teaching, demand driven research and community services and quality clinical services nationally and well- well organized college in East Africa by 2020 E.C

MISSION

The college committed to work being engaged in provision of effective teaching and learning , research and community services as well as quality clinical services to the society and to provide its innovative educational philosophy of community based education (CBE) in areas of excellent in academic and professional competence , research adoption ,innovation and knowledge /technology transfer

STRATEGIC THEMES

• Excellent in academic and professional competence
• Excellent in research adoption , innovation and knowledge /technology transfer
• Excellent in quality clinical service
• Excellent in service in different aspects of administration and development issues

ለ2018 ዓ.ም መስቀል በዓል እንኳን  አደረሳችሁ  በማለት  ከተማሪዎች  ጋራ  በደስታ ተከብሯል ።=========የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬ...
27/09/2025

ለ2018 ዓ.ም መስቀል በዓል እንኳን አደረሳችሁ በማለት ከተማሪዎች ጋራ በደስታ ተከብሯል ።
=========
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር፥ ዶክተር ወኪል ወልዴ እንዲሁም የተማሪዎች አገልግሎት ዲን መምህር መለሰ ማላቆን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተማሪዎችን እንኳን ለ2018 ዓ.ም መስቀል በዓል በሠላም አደረሳችሁ እያሉ በዓሉን ከተማሪዎች ጋራ በደስታ አክብሯል።

ተማሪዎች ፣ የተማሪዎች አገልግሎት ዘርፍ ሠራተኞች ፤ የተቋሙ የበላይ ኃላፊዎቻችን እንዲህ በበዓላት በአባትነት መንፈስ ሲጠይቁን ያስደስተናል ሲሉ ተናግረዋል ።

መልካም የመስቀል በዓል ።
በዓሉ የሠላም ፣የጤናና የፍቅር ይሁንልን

ዘገባው የኮሌጁ ኮሙኒኬሽንና ሕዝብ ግንኘነት ነው ።..... መስከረም 17/2018

በምክትል ፕረዚዳንት ማዕረግ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶክተር ወኪል ወልዴ ፥ለመስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።...
26/09/2025

በምክትል ፕረዚዳንት ማዕረግ
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶክተር ወኪል ወልዴ ፥ለመስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።
===
ዶክተር ወኪል ''የተከበራችሁ የኮሌጃችን የክርስትና ዕምነት ተከታይ ክሊኒካል፣ አካዳሚክና አስተዳደር ስታፍ እንዲሁም ደንበኞቻችን በሙሉ ፡

''እንኳን ለመስቀል በዓል በሠላም፤ በጤና አደረሳችሁ! አደረሰን !''

''በዓሉ ፥ ፍቅር የሚገለፅበት ፣ ወዳጅነት የሚጠነክርበት፣ አንድነት የሚጎለብትበት እንዲሆን እመኛለሁ'' ሲሉ መልካም ምኞታቸውን ገለፁ ።

ዶክተር በድጋሚ ፥በዓሉ የሰላም ፣ የፍቅር ፣ የጤና እና የአብሮነት እንዲሆን ተመኝተዋል ።

መስከረም 16/2018 ዓ.ም፧

መድኃኒትን የተላመደ ቲቪ ( Drug Resistant ,DR TB) ሕክምና በተመለከተ የባለድርሻ አካላት የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርትና ውይይት  ተካሂዷል።======== ቲቪ በሽታ ፥መከላከል የምን...
20/09/2025

መድኃኒትን የተላመደ ቲቪ ( Drug Resistant ,DR TB) ሕክምና በተመለከተ የባለድርሻ አካላት የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርትና ውይይት ተካሂዷል።
========
ቲቪ በሽታ ፥መከላከል የምንችለውና በተገቢው ሕክምና ክትትል ማዳን የሚቻል በሽታ እንደሆነ ባለሙያዎች ይናገራሉ ።
----------
በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲው ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ኮምፕርሄንሽቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የቲቪ ሕክምና አገልግሎት አሠጣጥ ለማሳለጥና ትኩረት ለመስጠት የ2017 ዓ.ም አራተኛ ሩብ እንዲሁም የ2018 በጀት ዓመት 1ኛ ሩብ ዕቅድ ክንውን ሪፖርትና የባለድርሻ አካላት ውይይት ተካሂዷል።

ዶክተር ታከለ ተክሉ ፦ በዩኒቨርስቲው ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የትምህርትና ጤና አገልግሎት ኮርፖሬት ዳይሬክተር በመድረኩ መክፈቻ ፥ የቲቪ በሽታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ተናግረዋል ።

አያይዘውም (Treatment Initiatation Center ,TIC) እዚሁ እንዲጀመር መነሻው ታካሚዎች ወደሌላ አካባቢ ሲሄዱ የሚገጥመውን እንግልትና ተግዳሮት ለማስቀረት ታልሞ እንደሆነ ገልፆ ፤ የዛሬው ውይይት የባለፈውን ዓመት አፈጻጸም ላይ በመነጋገርና ቀጣይ ሕክምናውን ለማሻሻልና ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ የባለድርሻ አካላት የውይይት መድረክ መሆኑን ተናግሯል ።

በውይይቱ የተለያዩ ጤና ተቋማት፥ የቦምቤ ፣ የዳሞት ጋሌ የዱቦ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጤና ተቋማት የቲቭ ሕክምና የአገልግሎት አሠጣጥ ተሞክሮ ፣ጥንካሬና እንዲሁም መሻሻል ባሉ ጉዳዮች ሪፖርት ቀርቦ ወይይት ተካሂዷል ።

ዶክተር ባካሎ በቀለ፥ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲው ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ኮምፕርሄንሽቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል መድኃኒት የተላመደ ቲቭ (DR-TB) TIC, አስተባባሪ ፥ መድኀኒት የተላመደ ቲቭ ፥ አለምአቀፋዊ ፣ ሀገራዊና አካባቢያዊ ጫና የዳሰሰ ገለፃ አቅረበዋል ።

አያይዞም በሽታውን የመለየትና የማከም አገልግሎት በትኩረት ማከናወን፤ ከታካሚዎች ጋር የቅርብ ግንኙነት ለነበራቸው ቅድመ ምርመራ ማድረግና በውጤቱ መሠረት ሕክምና መጀመር መከላከል መሆኑን አጽንኦት ሰጥቷል።
አያይዘውም ለበሽታው ተጋላጭ የሆኑ የማሕረሰብ ክፍሎችን ማለትም የስኳር እና የካንሰር ሕሙማንን እንዲሁም ሌሎች ቅድመ ምርመራና በሽታው ከታየባቸው ማከም ተገቢ መከላከያ መንገድ እንደሆነ ገልጸዋል።

ሲስተር ተስፋገነት ኢሳያስ በሆስፒታሉ የቲቪ ሕክምና ፎካል በበኩላቸው የሆስፒታሉን የ2017 ዓም የመጨረሻ ሩብ እንዲሁም የ2018 በጀት ዓመት የ1ኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና ቀጣይ ትኩረት አስመልክተው ሪፖርት አቅረበዋል ።

በመድረኩ የወላይታ ዞን ጤና መምሪያ ቲቪ ፎካል ጨምሮ ከዞኑ ከተለያዩ ጤና ተቋማት የተወጣጡ የቲቪ ሕክምና ፎካሎች ተሳትፈው ቀጣይ ውጤታማ አገልግሎት በዘርፉ ለመስጠት ጠቃሚ የጋራ መግባባት ተካሂዷል።

👉 ኮሙኒኬሽንና ሕዝብ ግንኙነት
መስከረም 2018 ዓ.ም

የማኔጅመንት አባላት እንኳን ለ2018 ዓ.ም አዲሱ ዓመት  በሠላም አደረሳችሁ  እያሉ በዓሉን ከተማሪዎች  ጋራ  አክብሯል ►►►►►►►►►►►የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌ...
11/09/2025

የማኔጅመንት አባላት እንኳን ለ2018 ዓ.ም አዲሱ ዓመት በሠላም አደረሳችሁ እያሉ በዓሉን ከተማሪዎች ጋራ አክብሯል
►►►►►►►►►►►
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር፥ ዶክተር ወኪል ወልዴ ፣ ትምህርትና ጤና አገልግሎት ኮርፖሬት ዳይሬክተር ዶክተር ታከለ ተክሉ እና አቶ ኢሳያስ አቦ፥ በኮሌጁ ኮርፖሬት ማኔጅንግ ዳይሬክተር በጋራ በተለያዩ የጤና ሙያ ከቅድመ አስከ ድሕረ ምረቃ እንዲሁም በሕክምና ስፔሻሊቲ ከመላ ሀገሪቱና ከምስራቅ አፍርካ ጭምር ትምርህታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ተማሪዎችን እንኳን ለ2018 ዓ.ም በሰላም አደረሳችሁ! በማለት በጋራ አክብረዋል ።

ማኔጅመንቱ፥ ሀገራችን ታላቁን የሕዳሴ ግድብ በስኬት አጠናቃ በርካታ ተስፋ ሰጪ ፕሮጀክቶችን ለመጀመር በዝግጅት ላይ ያለች በመሆኑ ተማሪዎች ባለራዕይና ተስፈኞች ሆነው ለሀገራችን ሠላምና ደኅንነት የበኩላቸውን እያበረከቱ ራዕያቸውን ለማሳካት ትኩረት እንዲያደረጉ አጽንኦት ሰጥቶ አሳስበዋል ።

በዓሉ የሠላም ፣ የፍቅር፣ የደስታና የስኬት እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

መጪው ጊዜ ለእኛ ብሩህ ነው ።

👉 የዘገበው የኮሌጁ ኮሙኒኬሽንና ሕዝብ ግንኙነት ቡድን ነው።

።።።።።።። መስከረም 1/2018 ዓ.ም።።።

🇪🇹 የአዲስ ዓመት 🇪🇹እንኳን  አደረሳችሁ መልዕክት ።።----የተከበራችሁ መላው የኮሌጃችን ማሕበረሰብ በሙሉ ፤---------አንኳን ለ2018 ዓ.ም አዲሱ ዓመት  በሠላም  በጤና አደረሳችሁ ...
10/09/2025

🇪🇹 የአዲስ ዓመት 🇪🇹እንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ።።
----
የተከበራችሁ መላው የኮሌጃችን ማሕበረሰብ በሙሉ ፤
---------
አንኳን ለ2018 ዓ.ም አዲሱ ዓመት በሠላም በጤና አደረሳችሁ ! አደረሰን !
=======
2018 ዓ.ም ዋዜማ ኢትዮጵያ የዘመናት የአይቻልም መንፈስ በልጆቿዋ በተባበረ ክንድና ዐቅም የሰበረችበት፣ በዓለም አደባባይ ከፍታዋን ባስመሰከረችበትና አዲስ ታርክ በሰራችበት ማግስት የሚከበር አዲስ ዓመት በመሆኑ፥ የታርኩ አካል በመሆናችን ትልቅ ደስታና ኩራት ይሰማኛል ።

በድጋሜ እንኳን ደስ አላችሁ ! እንኳን ደስ አለን!

ምንም ያህል ችግር ፈተና ቢፈራረቅ ፥ የዓላማ ጽናትና አንድነት ፣ ቅንጅትና መተባበር በሀሳብም በተግባር ካለን፥ የማንፈነቅለው ድንጋይ ፣ የማናልፈው ችግርና ተግዳሮት እንደሌለ ሕዳሴ ማሳያ ነው ።

በዘመናት መካከል አዳዲስና መልካም ነገሮች የፈለቁት ከፈተናዎች በላይ አሻግሮ በማየት ወደ አውንታዊ ዕድል በመቀየር፤ ለተግባራዊነቱ በጋራ በመሥራት አዲስ ዕይታን ተግባራዊ በማድረግ መሆኑ እሙን ነው ።

የተከበራችሁ መላው የኮሌጃችን ማሕበረሰብ ፤ ዛሬም ሀገራዊ ሆነ ተቋማዊ ማንኛውንም ተግዳሮት ለመሻገር ፤ አሠራርና አገልግሎት አሠጣጥ ለማሻሻልና ለማዘመን፣ አብሮነት ፣ አውንታዊ አስተሳሰብ ፣ መደጋገፍና መቻቻል አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው እያልኩ ፤ መጪው አዲስ ዓመት ለሀገራችን ንጋት ፣ ተስፋና ዕድገት ብልጽግና እውን የሚሆንበት እንዲሁም ለተቋማችንና ለሕዝባችን የሚገባው አዲስና መልካም ነገር የሚጀመርበት፤ የሚከወንበት ጊዜ እንዲሆን እመኛለሁ ።

አንኳን አደረሳችሁ! እንኳን አደረሰን !
በዓሉ የሰላም ፣ የደስታና የፍቅር ይሁንልን ።
🇪🇹 ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ !

ዶክተር ወኪል ወልዴ ፦በምክትል ፕረዚዳንት ማዕረግ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ።..... ጳጉሜ ❺/⓴⓱ ዓ.ም

እናመሰግናለን! አቶ ሔኖክ ደስታ  የChildren cross connection ድርጅት ሥራ አስኪያጅ ኦቶና አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልን መልሶ ለማደራጀት የገንዘብ ድጋፍ አደረጉ። 🙏🙏🙏🙏🙏...
09/09/2025

እናመሰግናለን!
አቶ ሔኖክ ደስታ የChildren cross connection ድርጅት ሥራ አስኪያጅ ኦቶና አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልን መልሶ ለማደራጀት የገንዘብ ድጋፍ አደረጉ።
🙏🙏🙏🙏🙏🙏
አቶ ሔኖክ በሆስፒታሉ በደረሰው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ማዘናቸውን ገልፀው ፤ ሆስፒታሉን መልሶ ለማደራጀት 50 ሺህ ብር ድጋፍ በማድረግ የበኩላቸውን አስተዋፅዖ አበርክተዋል።

አቶ ሔኖክ ይህ የመጀመሪያ ዙር የገንዘብ ድጋፍ ሲሆን፤ ቀጣይ በገንዘብና በዓይነት ድጋፋችን ይቀጥላልም ብለዋል ።

ዶክተር ወኪል ወልዴ ፦በምክትል ፕረዚዳንት ማዕረግ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ድጋፉን ተቀብለው ፥ድርጅቱ ላደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል ።
እናመሰግናለን።

ለመላው  የእስልምና እምነት ተከታይ  ወገኖቼ በሙሉ፤ እንኳን ለ1500ኛው የመውሊድ በዓል በሠላምና በጤና አደረሳችሁ!   በዓሉ የሰላም እና የፍቅር እንዲሆንላችሁ መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ።...
04/09/2025

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታይ ወገኖቼ በሙሉ፤
እንኳን ለ1500ኛው የመውሊድ በዓል በሠላምና በጤና አደረሳችሁ!

በዓሉ የሰላም እና የፍቅር እንዲሆንላችሁ መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ።

ዶክተር ወኪል ወልዴ፦ በምክትል ፕረዝዳንት ማዕረግ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር

መልካም በዓል!

01/09/2025
01/09/2025

የጤና አገልግሎት ስርዓቱን ሙሉ ለሙሉ በዲጂታል ሥርዓት እንዲመራ የሚያስችል ተግባር እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 26/2017 (ኢዜአ)፡-የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የጤና አገልግሎት ስርዓቱን ሙሉ ለሙሉ በዲጂታል ሥርዓት እንዲመራ የሚያስችል ተግባር እያከናወነ መሆኑን ገለጸ።

በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጅ ሚኒስቴር፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ በባዮ ቴክኖሎጂ ኢንስቲቱዩት እና በአፍሪካ ሲዲሲ ትብብር አለም አቀፍ የ "አሚክስ" ቴክኖሎጅ (AMICS) ኮንፈረንስ ዛሬ ተካሒዷል።

በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጅ ሚኒስቴር የሚኒስትሩ የቴክኖሎጂ አማካሪ ስሜነው ቀስቅስ (ዶ/ር) በወቅቱ፤ "አሚክስ" (AMICS) ማለት የሴሎችና የፕሮቲኖች ቅንጣቶች ናቸው ብለዋል፡፡

የ"አሜክስ" ቴክኖሎጂ ማለት ደግሞ እነዚህን የሴሎችንና የፕሮቲኖች ቅንጣቶችን ለመመርመር የሚረዳ መሳሪያ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

መንግስት ባለፉት ዓመታት ቴክኖሎጂን ማዕከል ያደረጉ በርካታ ስራዎችን በመስራቱ በሁለንተናዊ ዘርፎች አመርቂ ውጤቶችን ማስመዝገብ መቻሉን ተናግረዋል፡፡

በዛሬው ዕለትም በተለይ የጤናው አገልግሎት ዘርፉን ከፍ ወዳለ ምዕራፍ በሚያሸጋግር በ"አሜክስ" ቴክኖሎጅ ጉዳይ ላይ ውይይት መደረጉን ገልጸዋል።

አሜክስ ቴክኖሎጂ የህክምና አይነት ሲሆን የዘረመል ምርመራዎችን ጨምሮ ክትባቶችንና ሌሎች መድሃኒቶችን በአገር ውስጥ እንዲካሔዱና እንዲመረቱ የሚያስችል ነው ብለዋል።

ሰዎች በሚታመሙበት ወቅት የሰውነት ንጥረ ነገሮቻቸውን መርምሮ ትክክለኛ መድሃኒት በትክክለኛ ወቅት ለማሰጠት እንደሚያግዝም እንዲሁ፡፡

ይህ ቴክኖሎጅ ወደ ኢትዮጵያ ከገባ የጤናውን ዘርፍ አገልግሎት እንደሚያልቀው ጠቁመው፣ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ቴክኖሎጂው እንዲገባ ከአለም አቀፍ ተመራማሪዎች ጋር በትብብር እንደሚሰራ ነው የተናገሩት።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዚዳንት ጄይሉ ኡመር (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የኮንፈረንሱ ዋና አላማ ዜጎች አለም የደረሰበትን የህክምና ቴክኖሎጂ እንዲጠቀሙ ለማድረግ ነው ብለዋል፡፡

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ "የአሚክስ" ቴክኖሎጂ ወደ ኢትዮጵያ ገብቶ አገልግሎት መስጠት እንዲጀምር በእውቀት ሽግግርም ሆነ በሌሎች ጉዳዮች ላይ የድርሻውን ለማበርከት ዝግጁ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

በአዲስ አበባ ዪኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ በባዮ ኬሚስትሪ ዲፓርትመንት የባዮ ኬሚስትሪ ተባባሪ ፕሮፌሰር ሰለሞን ተበጅ በበኩላቸው፤ የአሚክስ ቴክኖሎጂው የጤና አገልግሎት ስርዓቱን የሚያልቅ ነው ብለዋል፡፡

ቴክኖሎጂው አካባቢን ቀድሞ በማወቅ ክትባቶችን ለማዘጋጅትና መዳህኒቶችን ለማምረት እንደሚረዳ ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ተሞክሮ የሚወሰድባቸው መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ በጃፓን ሆካዶ የኒቨርሲቲ ተባባሪ ፕሮፌሰር ሲዳባሳቭ ጎወአ ናቸው፡፡


#ኢዜአ

#ኢትዮጵያ

01/09/2025
01/09/2025
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከራዲዮ ኢትዮጵያ ግብረሰናይ ድርጀት ጋር በመሆን የክረምት የጤና በጎ አድራጎት ሥራ መስጠት ጀመረ።   ነጻ ምርመራው  ከዛሬ ነሐ...
01/09/2025

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከራዲዮ ኢትዮጵያ ግብረሰናይ ድርጀት ጋር በመሆን የክረምት የጤና በጎ አድራጎት ሥራ መስጠት ጀመረ።

ነጻ ምርመራው ከዛሬ ነሐሴ 26/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለአንድ ሳምንት የሚቆይ ሲሆን፤ 10 ሺህ ሰዎችን ተጠቃሚ ለማድረግ የታቀደ መሆኑ ተገልጿል ።

''በጎነት ለጤናችን '' በሚል ለአንድ ሳምንት የሚሰጥ ሲሆን በዚህ በጎ አድርጎት ነፃ የጤና ምርመራ ፣ የጤና አጠባበቅ ትምህርትና የምክር አግልግሎት ይሰጣል ።

በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ወኪል ወልዴ ይህ የጤና በጎ አድራጎት ሥራ 3 ዓመት ማስቆጠሩንና ይህ የነፃ የጤና ምርመራ እስከ ጳጉሜ መጨረሻ እንደሚቀጥልና በዚህ አግልግሎት 10 ሺህ ሰዎችን ለመድረስ መታቀዱንና ማንኛውም ግለሰብ የነፃ አግልግሎቱን ማግኘት እንደሚችል ተናግረዋል።

የራዲዮ ኢትዮጵያ ግብረሰናይ ድርጀት ዶ/ር ልሳነወርቅ ሆንሴቦ በጎነት ድርጀቱ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት በማስቀደም በጤና ፣ በትምህርት በወጣቶችና ህፃናት እንዲሁም በአከባቢ ጥበቃ ላይ ትኩረት አድረጎ እንደሚሰራ ገለፀዋል። ይህን የበጎ አድራጎት ስራ ከሆስፒታሉ ጋር በመተባበር መዘጋጀቱንና በበጎ ፈቃደኛ የጤና ባለሙያዎች ነፃ የስኳር በሽታ ፣ የደም ግፊት ምርመራና የጤና አጠባበቅ ትምህርት እንደሚሰጥ ገለፀዋል።

አግልግሎቱን ያገኙ ግለሰቦች ለተደረገላቸው ህክምና በማመስገን ህብረተሰብ በእንደዚህ ዓይነት በነፃ ህክምና በመውሰድ ራሱን እንዲያውቅና የመመርመር ልማድ ማሳደግ እንዳለበት አንስተዋል።

Address

Wolaita
Sodo

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when WSU College of Health Science and Medicine - ወሶዩ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to WSU College of Health Science and Medicine - ወሶዩ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram