Bele primary hospital-በሌ አዋሳ

Bele primary hospital-በሌ አዋሳ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Bele primary hospital-በሌ አዋሳ, Hospital, በሌ አዋሳ, Sodo.

ወቅቱን ጠብቆ የሚመጣዉን የኮሌራ ወረርሽኝና የወባ በሽታን ለመግታትና ለመቆጣጠር በጋራ መስራት እንደሚገባ ተጠቆመ በሌ አዋሳ፤ ነሐሴ 15/2015 በበሌ አዋሳ ከተማ አስተዳዳር ጤና ዩኒቲ የኮ...
21/08/2023

ወቅቱን ጠብቆ የሚመጣዉን የኮሌራ ወረርሽኝና የወባ በሽታን ለመግታትና ለመቆጣጠር በጋራ መስራት እንደሚገባ ተጠቆመ

በሌ አዋሳ፤ ነሐሴ 15/2015 በበሌ አዋሳ ከተማ አስተዳዳር ጤና ዩኒቲ የኮሌራ በሽታና የወባ በሽታን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር ያለመ ከተማዊ ንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል።

የኮሌራ በሽታ እና የወባ በሽታ በህብረተሰቡ ጤና ላይ የሚደርሰው ጉዳት እጅግ ከፍተኛ መሆኑን የገለጹት የበሌ አዋሳ ከተማ አስ/ር የመንግስት ዋና ተጠሪ ዶ/ር አባይነህ አጫ በሽታዉ እንዳይዛመት እና እንዳይስፋፋ የሁላችንም ሚና ከፍተኛ ልሆን ይገባል ብለዋል።

አክለዉም ዶ/ር አባይነህ አጫ አከባቢያችን ቆላማ ከመሆኑም አንጻር በስፋት የሚስተዋለዉን የወባ በሽታ ለመከላከል በህብረተሰቡ ዘንድ የአልጋ አጎበር አጠቃቀም ልስተካከል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በሽተዉን ለመከላከል ከንጽህና ጉድለት ጋር የተያያዙ ችግሮችን መቅረፍ እንደሚገባ ያሳሰቡት ዶ/ር አባይነህ አጫ ምግብ ቤቶች፣ እንዲሁም መጸዳጃ ቤቶች በአግባቡና በንጽህና መጠቀም እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል።

የበሌ አዋሳ ከተማ አስ/ር ም/ከንቲባና ኢኮኖሚ ክለስተር አስተባባሪ አቶ ተመስገን ፎላ ወረርሽኙ በፍጥነት የሚዛመት ስለሆነ ቀድመን ለመቆጣጠርና ለመከላከል አስፈላጊውን ስራ በጋራ መስራት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።

አያይዘዉም አቶ ተመስገን ፎላ ከጤና የሚተላለፉ መልእክቶችን የመረጃ ፍሰትን በጠበቀ መልኩ በደንብ ማዳመጥና ተግባር ላይ ማዋል ብሎም ማህበረሰቡን መታደግ ይገባል ብለዋል።

በበሽታዉ በአንድ ግለሰብ ከተያዘ ከአንድ እስከ አራት ሳምንት ድረሰ ምንም አይነት ምልክት ላሳይ ስለምችል ህብረተሰቡ በሽታ አምጪ ናቸዉ ተብሎ በጤና ኤክስተሽን በኩል የሚሰጡ ትምህርቶችን ተግባራዊ በማድረግ በሽታዉን ልከላከል ይገባል ብለዋል።

ኮሌራን ጨምሮ የዘርፈ ብዙ ወረርሽኝ በሽታ መከላከል ግብረ ሃይል አደረጃጀት፣ ተግባርና ኃላፊነትን አስመልክቶ በተዘጋጀው ሰነዶች በጤና ዩኒቲ አቶ ተስፋዬ ኡርቼ ያቀረቀበ ስሆን ሰፋ ያለ ዉይይት ተደርጎበት ተደርጎበታል።

በመጨረሻም ዶ/ር አባይነህ አጫ የኮለራ በሽታንም ሆነ የወባ በሽታን የቅደመ መከላከል ተግባራት ከፈጸምን ምንም አይነት አስከፊ ጉዳት ሳይደርስ ልቆጣጠረዉ የምንችለዉ ነገር ስለሆነ ሁላችን ቅንጅታዊ አሰራርን በመዘርጋት በጋራ ልንሰራ ይገባል ብለዋል

በመድረኩ የከተማ አስተባባሪ አካላት፣ የከተማ እና የቀበሌ አመራሮች፣ የከተማ ጤና ዩኒቲ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች እንድሁም የጤና ኤክስቴንሽን ባለሞያዎችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

21/01/2023

Address

በሌ አዋሳ
S**o

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bele primary hospital-በሌ አዋሳ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram

Category