06/01/2026
የጌታችን የመድሐኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓልን በማስመልከት ከእንሳሮ ወረዳ ጤና ፅህፈት ቤት ሃላፊና የእንሳሮ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ውብሸት ሙልዬ የተላለፈ የእንኳን አደረሳችሁ መልካም ምኞት መግለጫ !!
በወረዳችን ለምትገኙ የክርስትና እምነት ተከታይ የሆናችሁ በሙሉ እንኳን ለጌታችንና ለመድሀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!!
የጌታችንና የመድሐኒታችን እየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በእየ አመቱ ታህሳስ 29 ቀን በታላቅ ድምቀት ከሚከበሩ ሀይማኖታዊ በዓላት መካከል አንዱ ነው፡፡
በዓሉ በቤተ ዕምነቱ እና በምዕመናኑ ዘንድ እጅግ ልዩ ትርጉም ያለው በብዙ ሀይማኖታዊ ስርዓቶች የሚከበር በዓል ነው፡፡
ስለሆነም መላው የዕምነቱ ተከታዮች እና ኢትዮጵያዊን ብዙ ትርጉም ባለው በዚህ በአል እንደከዚህ ቀደሙ በመቻቻል ፣ በመፈቃቀር እና በአንድነት እንድናከብር እያልኩ በወረዳችን ለምትገኙ የክርስትና እምነት ተከታይ በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለመድሐኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን እያልን ፡-
የእንሳሮ ወረዳ ጤና ፅህፈት ቤት ሃላፊና የእንሳሮ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ዉብሸት ሙልዬ
ታህሳስ 2018 ዓ/ም