Ethiopian Orthodox Tewahedo Medical Association

Ethiopian Orthodox Tewahedo Medical Association Nonprofit organization inspired by Faith, Hope and LOVE to provide a compassionate care for humanity

ከ 6.5 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የሕክምና አገልግሎት ተሰጠ4ኛው ዓመታዊው "መጻጉዕን በመቄዶንያ" ነጻ የሕክምና አገልግሎት ተጠናቀቀ።የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር በየዓመ...
03/17/2026

ከ 6.5 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የሕክምና አገልግሎት ተሰጠ
4ኛው ዓመታዊው "መጻጉዕን በመቄዶንያ" ነጻ የሕክምና አገልግሎት ተጠናቀቀ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር በየዓመቱ የሚያደርገውን "መጻጉዕን በመቄዶንያ" ነጻ የሕክምና አገልግሎት ከየካቲት 29 እስከ መጋቢት 6 ለተከታታይ 8 ቀናት ሲያካሂድ ቆይቶ በተሳካ ሁኔታ ለማጠናቀቅ ቻለ።
በዚህ አገልግሎት ዘርፈ ብዙ የሕክምና አገልግሎት ከተሟላ ላቦራቶሪ እና ዲያግኖስቲክ ምርመራ ጋር ለመስጠት ተችሏል።
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የዓይን ሕክምና ክፍል ጋርም በመተባበር ለ 293 ሰዎች የዓይን ሕክምና የተሰጠ ሲሆን 54 የዓይን ሞራ ግርዶሽ (Cataract) ተጠቂ የሆኑ ታካሚዎች ተለይተው የቀዶ ሕክምና አገልግሎት ለመስጠት ተዘጋጅተዋል።

በጥርስ ሕክምና ባለሙያዎችም የተሟላ የጥርስ ሕክምና እንዲሁም የጥርስ ነቀላ (Dental extraction) ለማድረግ ተችሏል።

የልብ ሕክምና የሚያስፈልጋቸው ታካሚዎችም በልብ ሐኪሞች የተሟላ ሕክምና የተሰጣቸው ሲሆን 30 ታካሚዎች የልብ አልትራሳውንድ (Echocardiograph) እና ECG ተሰርቶላቸዋል።

በ ኢንተርናሽናል ክሊኒካል ላቦራቶሪ (ICL) ለ 1000 ታካሚዎች እንዲሁም በ አርሾ ሜዲካል ላቦራቶሪ ደግሞ ለ 150 ታካሚዎች የተሟላ የላቦራቶሪ ምርመራ ለማድረግ ተችሏል።
በተጨማሪም የፊዚዮቴራፒ እና የደረቅ መርፌ (Acupuncture) ሕክምና በባለሙያዎች የተሰጣቸውም ይገኙበታል።

በዚህ አገልግሎት ከተለያዩ የሕክምና ስፔሺያሊቲ እና የጤና ሙያ የተውጣጡ ከ160 በላይ ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ 50 ስፔሺያሊስት፣ 6 ሰብስፔሺያሊስት ሐኪሞች ፣ 44 ጠቅላላ ሐኪሞች፣ 30 ነርሶች፣ 8 የጥርስ ሐኪሞች፣ ፋርማሲስቶች፣ ፊዚዮቴራፒስቶች፣ የስነእምሮ እና የማኀበረሰብ ጤና ባለሙያዎች እንዲሁም የላቦራቶሪ ቴክኒሺያኖች ይገኙበታል።

በ4ኛው ዓመታዊው "መጻጉዕን በመቄዶንያ" ነጻ የሕክምና አገልግሎት ባጠቃላይ 1070 ታካሚዎች የተለያዩ የሕክምና አገልግሎቶች ተጠቃሚ ሲሆኑ አጠቃላይ የተሰጠው የሕክምና አገልግሎትም በገንዘብ 6,502,115 ብር የሚገመት ነበር።
ለዚህ አገልግሎት መሳካት የረዳችሁንን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የዓይን ሕክምና ክፍል ፣ ኢንተርናሽናል ክሊኒካል ላቦራቶሪ (International clinical laboratories)፣ አርሾ ሜዲካል ላቦራቶሪ (Arsho medical labratories P.L.C) ፣ ያኔት አጠቃላይ ሆስፒታል (Yanet General Hospital)፣ ዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል (Zewditu Memorial Hospital)፣ ኦቶሪኖ ልዩ የአንገት በላይ ክሊኒክ (Otorino Ent Surgical Center) ፣ Badreg Pharmaceuticals እና ELPIS PHARMACEUTICALS በአገልግሎቱ ተጠቃሚ በሆኑት ወገኖቻችን ስም ለማመስገን እንወዳለን። ለጤና ባለሙያዎችም የምግብ አቅርቦት ድጋፍ ላደርጉልን ROMi Catering & Restaurant ከልብ እናመሰግናለን።

በዚህ የበጎ ፈቃድ የሕክምና አገልግሎት ለሳተፉት ባለሙያዎች እና ለአገልግሎቱ መሳካት ድጋፍ ላደረጉ ድርጅቶች የምስጋና ምስክር ወረቀት የተሰጠ ሲሆን፤ ጊዜያችሁን እና ሙያችሁን በነጻ ለወገናችሁ በመለገስ ለሰጣችሁት አገልግሎት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር ለማመስገን እንወዳለን።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር
“አክብሮትና ትህትናን የተላበሰ የጤና አገልግሎት ለሰው ልጆች በሙሉ”

Congratulations to Our Newly Matched Physicians!Today we proudly celebrate members of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Me...
03/16/2026

Congratulations to Our Newly Matched Physicians!

Today we proudly celebrate members of the
Ethiopian Orthodox Tewahedo Medical Association (EOTMA)
who successfully matched into residency programs through the
National Resident Matching Program (N**P) on Match Day — March 16, 2026.

After years of dedication, perseverance, and commitment to the healing profession, these outstanding physicians have reached an important milestone in their medical journey.

Your achievement reflects not only academic excellence but also a deep calling to serve humanity with compassion, integrity, and faith.

As you begin residency training, we pray that God grants you wisdom, strength, and humility as you care for patients and advance the noble mission of medicine.

We are incredibly proud of you and look forward to the impact you will make in healthcare and in our communities.

May God bless your journey ahead.

Congratulations, Doctors!

03/07/2026

ለ “4ኛው ዓመታዊው መጻጉዕን በመቄዶንያ” አገልግሎት የተመዘገባችሁ የሕክምና ባለሙያዎች ለበጎ ፈቃደኝነታችሁ ከወዲሁ እያመሰገንን ፤ አገልግሎቱ የሚጀመረው ነገ ስለሆነ በተመዘገባችሁት ቀን እና ሰዓት በቦታው በመገኘት የአገልግሎቱ ተሳታፊ እንድትሆኑ አደራ እንላለን።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር

4ኛው ዓመታዊው መጻጉዕን በመቄዶንያ ነጻ የሕክምና አገልግሎት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር በየዓመቱ የሚያደርገውን "መጻጉዕን በመቄዶንያ" የተሰኘውን ነጻ የሕክምና አገልግሎት...
02/26/2026

4ኛው ዓመታዊው መጻጉዕን በመቄዶንያ ነጻ የሕክምና አገልግሎት

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር በየዓመቱ የሚያደርገውን "መጻጉዕን በመቄዶንያ" የተሰኘውን ነጻ የሕክምና አገልግሎት 4ኛ ዙር ዘንድሮም ከተለያዩ የሕክምና ስፔሺያሊቲ እና የጤና ሙያ በተውጣጡ ባለሙያዎች ከ የካቲት 29 - መጋቢት 6 (March 8 - 15 ) ለ 8 ቀን የሚቆይ አገልግሎት ይሰጣል። በዚህ አገልግሎት ለመሳተፍ የምትፈልጉ ከዚህ በታች የተዘረዘሩ ባለሙያዎች የምዝገባ ቅጹን በመሙላት አውንታችሁን እንድታሳውቁን በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን።

ቀን፡ የካቲት 29 - መጋቢት 6 // Date: March 8 - March 15

ሰዓት፡ ከጠዋቱ 2፡30 - 11:00 ሰዓት // Time: 8:30 AM - 5:00 PM

ቦታ፡ መቄዶንያ የአረጋውያንና አእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል

ለዚህ አገልግሎት የሚያስፈልጉ ባለሙያዎች የሚከተሉት ናቸው፦

Specialties needed are:
General Practitioners
Internal Medicine
Cardiology
Nursing
Dentists
Dermatology
Pharmacists
Ophthalmology
Public Health Experts
ENT
Orthopedics
Urology
Neurology
Neurosurgery
Social Worker
Mental Health
Psychiatry
Health Officers
General Surgery
Laboratory Technicians
Physiotherapists

ጥያቄ ካለዎት በ 0944111990 ይደውሉ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር

“አክብሮትና ትህትናን የተላበሰ የጤና አገልግሎት ለሰው ልጆች በሙሉ”

https://forms.gle/2ozP8vAh2dfy5sRV6

የአደባባይ በዓላት ድንገተኛ ሕክምና አገልግሎት ክፍል በጥምቀት በዓል ላይ አገልግሎት ሰጠ።የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር የአደባባይ በዓላት ድንገተኛ ሕክምና አገልግሎት ክፍል ...
01/20/2026

የአደባባይ በዓላት ድንገተኛ ሕክምና አገልግሎት ክፍል በጥምቀት በዓል ላይ አገልግሎት ሰጠ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር የአደባባይ በዓላት ድንገተኛ ሕክምና አገልግሎት ክፍል በየዓመቱ እንደሚያደርገው በጥምቀት በዓል ላይ በመገኘት አገልግሎት ለመስጠት ችሏል።

በዚህም አገልግሎት ከተለያዩ ስፔሺያሊቲ የተውጣጡ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር በዕለቱ በበጎ አገልግሎት ለተሳተፉ የጤና ባለሙያዎች የላቀ ምስጋና ለማቅረብ ይወዳል።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር የአደባባይ በዓላት ድንገተኛ ሕክምና አገልግሎት ክፍል የአደባባይ በዓላት ላይ እና ህዝብ በሚበዛባቸው ክስተቶች (Public events) ላይ የድንገተኛ ሕክምና አገልግሎት መስጠት ከጀመረ 5 ዓመታትን ያስቆጠረ ሲሆን በዚህም አገልግሎት ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ባለሙያዎች ተሳትፈዋል ብዙዎችም የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ለመሆን ችለዋል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር ለሁሉም በሁሉም!
# eotma_for_all_by_all

እንኳን ለብርሃነ ልደቱ አደረሳችሁ!" ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና፤ አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል፤ ስሙም ድንቅ መካር፥ ኃያል አምላክ፥ የዘላለም አባት፥ የሰላም አለቃ ...
01/06/2026

እንኳን ለብርሃነ ልደቱ አደረሳችሁ!

" ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና፤ አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል፤ ስሙም ድንቅ መካር፥ ኃያል አምላክ፥ የዘላለም አባት፥ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል።" ኢሳይያስ 9፡6

Happy Nativity Feast!

"For unto us a child is born, unto us a son is given: and the government shall be upon his shoulder: and his name shall be called Wonderful, Counsellor, The mighty God, The everlasting Father, The Prince of Peace." Isaiah 9:6

የስራ ማስታወቂያየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር ከዚህ በታች የተጠቀሱትን የጤና ባለሙያዎች አወዳድሮ በቋሚነት መቅጠር ይፈልጋል።
10/09/2025

የስራ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር ከዚህ በታች የተጠቀሱትን የጤና ባለሙያዎች አወዳድሮ በቋሚነት መቅጠር ይፈልጋል።

🎉 Congratulations! 🎉We proudly extend our heartfelt congratulations to Dr. Tsebelu Shirshawa on being recognized as the ...
06/26/2025

🎉 Congratulations! 🎉

We proudly extend our heartfelt congratulations to Dr. Tsebelu Shirshawa on being recognized as the Best PGY-I Categorical Resident by the Howard University Hospital Department of Medicine – Internal Medicine Residency Program.

Dr. Tsebelu, a dedicated member of EOTMA, matched into his residency program during last year’s match season. His recognition reflects his exceptional performance, professionalism, and commitment to excellence in patient care and medical training.

This achievement is not only a personal milestone but also an inspiration to our EOTMA community. We are honored to support members like Dr. Tsebelu who continue to set a high standard in their medical journey.

Congratulations, Dr. Tsebelu— we celebrate your success and look forward to your continued accomplishments!

ዶ/ር ፀበሉ ለዚህ እውቅና እና ሽልማት ስለበቃህ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር እንኳን ደስ አለህ ለማለት እንወዳለን።

እንኳን ደስ አላችሁ!🎉 Congratulations! 🎉We are thrilled to celebrate the success of Dr. Helina M. Bzuayehu and Dr. Henok Ayalew...
06/26/2025

እንኳን ደስ አላችሁ!
🎉 Congratulations! 🎉

We are thrilled to celebrate the success of Dr. Helina M. Bzuayehu and Dr. Henok Ayalew Tafesse, esteemed members of EOTMA, on their remarkable achievement!

Both doctors have successfully matched into Internal Medicine residency programs in the United States during the 2025 Match Season and will begin their training on July 1, 2025.

🎉Dr. Helina M. Bzuayehu will be joining the Internal Medicine residency at Campbell University Cape Fear Valley Medical Center in Fayetteville, North Carolina.

🎉 Dr. Henok Ayalew Tafesse will begin his Internal Medicine residency at Morehouse School of Medicine in Atlanta, Georgia.

This milestone reflects their dedication, resilience, and excellence in the field of medicine.

At EOTMA, we are proud to offer mentorship and support programs for members pursuing advanced medical training in the USA, including ECFMG certification and the residency application process via ERAS.

We also invite aspiring medical students and professionals to join our Student Chapter, where they can gain valuable academic and clinical experience through volunteer opportunities and mentorship.

Please join us in congratulating Dr. Helina and Dr. Henok on this exciting new chapter.

We wish them continued success in their medical careers!

እንኳን ደስ አላችሁ ዶ/ር ህሊና ብዙአየሁ እና ዶ/ር ሔኖክ ታፈሰ!

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር አባላት ዶ/ር ህሊና ብዙአየሁ እና ዶ/ር ሔኖክ ታፈሰ ለሬዚደንስ ፕርግራም እድሉን በማግኘታችሁ እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን።

https://www.facebook.com/share/p/19wSEW4wnV/?mibextid=WC7FNe
05/04/2025

https://www.facebook.com/share/p/19wSEW4wnV/?mibextid=WC7FNe

አጭር የህይወት ታሪክ
(የቀጠለ.....)
ሆስፒታል ማቋቋም ብቻውን በዘርፉ ያለውን ችግር መቅረፍ እንደማይችል በማመን በርካታ የህክምና ባለ ሙያዎችን በራሳቸው /በዶ/ር ፍቅሩ/ ወጪ ስዊድን ድረስ በመላክ በልብ ህክምናው ስፔሻላይዝድ ያደረጉ እውቅ ሀኪሞችን በማፍራት የሰለጠነውን አለም የህክምና ሙያ ወደ ሀገር በማምጣት ለእውቀት ሽግግር ብርቱ ዋጋ ከፍለዋል። በዚህም በሰለጠነው አለም ብቻ ይሰጥ የነበረውን ውስብስብ የተባለ የልብ ህክምና ወደ ሀገራችን በማምጣት ጉልህ ሚና የተጫወቱ የሀገር ባለውለታ ናቸው, ካርዲዮሎጂስቱ ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ፡፡ ለወትሮው ህክምናውን ፍለጋ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ወደ ውጪ ይደረግ የነበረውን ጉዞ በማስቀረት ባለፉት ሁለት አስርት አመታት ሀገሪቱ ልታወጣ የምትችለውን የውጭ ምንዛሪ በማስቀረት አሻራቸውን ያኖሩት ዶ/ር ፍቅሩ፤ በአዲስ ካርዲያክ የማይሰጡ የልብ ህክምናዎች የሚደረግበትን ታዝማ የውስጥ ደዌ እና የቀዶ ልዩ ህክምና ማዕከልንም በመመስረትና አሁን ለደረሰበት ደረጃ
በማብቃት ዛሬ በርካታ ህፃናትና ወጣቶችን በልብ ህክምና እጦት ምክንያት ከሚነጥቀው ሞት መታደግ የቻሉ ታላቅ የሃገር ባለውለታ ናቸው።በጥቁር አንበሳ የሚሠጠውን የልብ ህክምና ለማዘመን ያላሰለሰ ጥረት ሲያደርጉ የቆዩት ዶ/ር ፍቅሩ በተለያዩ ጊዜያት በውድ ዋጋ የሚገዙ አላቂ የህክምና መሳሪያዎችን በእርዳታ በማቅረብ በርካታ አስተዋፆ አበርክተዋል።የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሲመሠረት በወቅቱ በነበሩት የጤና ሚኒስቴር ተመርጠው በተጣለባቸው ሃገራዊ ኃላፊነት መሠረት የግል የጤና ተቋማትን በማስተባበር ከመቶ ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ እንዲሰበሰብ በማድረግ ደማቅ አሻራቸውንም አኑረዋል። በጦርነቱ ወቅት የተጎዱ ት/ቤቶችንና ተቋማትን ለማገዝ በሚደረግ ርብርብ ውስጥ ሰፊ አበርክቶ የነበራቸውም ታላቅ ሰው ነበሩ።''በሀገርና በህዝብ ቂም የለም'' የዶ/ር ፍቅሩ ፅኑ እምነት ነው።ለሃገራቸው ፅኑ ፍቅር ያላቸው ዶ/ር ፍቅሩ ባለፈው ስርዓት በተለያየ ወቅት ለእስር ተዳርገዋል፡፡ ታድያ ስርዓተ ለውጡን ተከትሎ ከእስር ቤት ሲወጡ ዜግነት ወዳላቸው ስዊድን ሀገር ለህክምና ይጓዛሉ። በዛን ወቅት ተመልሰው አይመጡም ተብሎ ብዙ ሲናፈስ እርሳቸው ግን በጥቂት ሳምንታት ነበር ወደ ሀገራቸው ተመልሰው የገቡት። 'ይሄ ሁሉ በደል ደርሶብዎ እንዴት ወደ ሀገርዎ ሊመለሱ ቻሉ?' ተብለው ሲጠየቁ ምላሻቸው አጭርና ግልፅ ነበር '' በሀገርና በህዝብ ቂም የለም" ነበር ምላሻቸው።
ላለፉት አስራ ዘጠኝ አመታት በኪራይ ቤት አገልግሎት ሲሰጥ የቆየውን አዲስ የልብ ህክምና በዘርፉ የሀገሪቱ የልህቀት ማዕከል ለማድረግ ከነበራቸው ጥልቅ ፍላጎት በመነሳት ለመኖሪያነት በገዙት መሬት ላይ ደረጃውን የጠበቀ ባለ ስምንት ወለል ህንፃ በመገንባት በቅርቡ ሆስፒታሉን ወደ አዲስ ምዕራፍ በማሸጋገር ሂደት ላይ ነበሩ።
ነገር ግን ባጋጠማቸው የጤና እክል ምክንያት በስዊድን ሀገር ህክምናቸውን ሲከታተሉ ቆይተው በተወለዱ በ74 አመታቸው ከዚህ አለም ድካም አርፈዋል።
ካርዲዮሎጂስት ዶ/ር ፍቅሩ ባለትዳርና የሁለት ሴት ልጆች አባት እንዲሁም የአራት የልጅ ልጆች አያት ነበሩ።
የዶ/ር ፍቅሩ ማሩ የቀብር ስነ-ስርዓት በስዊድን ሀገር የሚፈፀም ሲሆን በሀገር ውስጥ ሀዘን መካፈል ለሚፈልጉ አዲስ አበባ ጃክሮስ እግዚአብሔር አብ ቤተ-ክርስቲያን አጠገብ - ከቪዥን ት/ቤት ጀርባ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው መድረስ የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
- ቤተሰቦቻቸው፣አዲስ የልብ ህክምና ሆስፒታል ማኔጅመንትና ሰራተኞች፤ታዝማ የውስጥ ደዌ እና የቀዶ ልዩ ህክምና ማዕከል ማኔጅመንትና ሰራተኞች ለቤተሰቦቻቸው እንዲሁም ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ

https://www.facebook.com/share/p/18uDWsMsbB/?mibextid=WC7FNe
05/04/2025

https://www.facebook.com/share/p/18uDWsMsbB/?mibextid=WC7FNe

አጭር የህይወት ታሪክ
በኢትዮጵያ በግል ህክምናው መስክ በሀገሪቱ የመጀመሪያ የሆነው የአዲስ የልብ ህክምና ሆስፒታል እና ታዝማ መስራች የሆኑት ካርዲዮሎጂስት ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ ከዚህ አለም ድካም ማረፋቸው ተገለፀ።
በአዲስ አበባ ፈረንሳይ ለጋሲዮን በተለምዶ ጉራራ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሺ ዘጠኝ መቶ አርባ ሶስት ዓ.ም የተወለዱት ካርዲዮሎጂስት ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ እድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ በኮከበ ፅባህ ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ት/ቤት የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል።
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውንም አሰላ በሚገኘው ራስ ዳርጌ ት/ቤት ተከታትለዋል።
በሺ ዘጠኝ መቶ ስልሳዎቹ መጀመሪያ ለሀገር ፍቅር ከነበራቸው ጥልቅ ስሜት በመነሳትም የኢትዮጵያ የአየር ኃይልነት ምልመላ ሲከናወን ትምህርታቸውን አቋርጠው የኢትዮጵያ አየር ኃይልን ተቀላቀሉ።
በወቅቱ አየር ኃይልን ለመቀላቀል ከተመለመሉ 27 እጩ አባላት መካከል በብቃት የአየር ኃይልነት ስልጠናን አጠናቀው በጀት አብራሪነት የተመረቁት 5 ብቻ ነበሩ፡፡ ከነዚህም ብቸኛው ጀት ስኳዶር ሆኖ የወጣው በዕድሜ ትንሹ የነበረው ፍቅሩ ማሩ ነበር።
በሺ ዘጠኝ መቶ ስልሳ ስድስት የአብዮቱን መፈንዳት ተከትሎ ደርግ ለስልጣኔ ስጋት ይሆናሉ ያላቸውን ግለሰቦች እያፈሰ ወደ እስር ቤት ማጋዝ ሲጀምር በሃገር ፍቅር ስሜት ተቆርቋሪነታቸው የሚታወቁትን የመቶ አለቃ ዶ/ር ፍቅሩንም ማሳደድ ይጀምራል፤ የህዝቦች እኩልነትና አንድነት ይረጋገጥ ዘንድ ይታገሉ የነበሩት ዶ/ር ፍቅሩም በደርግ እየታሰሱ መሆናቸውን ሲረዱ የሚወዱትን ሃገር ጥለው ወደ ሱዳን ይሰደዳሉ። ከዛም ወደ ስዊድን በመሻገር የስደት ህይወትን ይጀምራሉ።
በወቅቱ እሳቸውን መያዝ ያልቻለው ደርግም ሁለት ወንድሞቻቸውን ይገድልባቸዋል።
በስዊድን ቆይታቸው በሃገራቸው የዲሞክራሲ ስርዓት እንዲገነባ በመላው አውሮፓ የሚገኙ የኢህአፓ የተማሪዎች ንቅናቄን በመምራት ጉልህ ሚናን ከመጫወታቸው በላይ በልብ ህክምናው ዘርፍ ስፔሻላይዝ በማድረግ በእስካንዴኔቪያን ሃገራት ጭምር አንቱታን ያተረፉ ካርዲዮሎጂስት ናቸው።
በሺ ዘጠኝ መቶ ዘጠናዎቹ መጀመሪያ የኤች አይ ቪ ቫይረስ ስርጭት እንደሃገር ስጋት በደቀነ ግዜ የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት ሃገራዊ ጥሪ ሲደረግ በስዊድን ያሉ አጋር ድርጅቶችን በማስተባበር ወደ ሃገር ቤት ቀድመው ከዘለቁ የሀገር ባለውለታ መካከል አንዱ ናቸው, ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ
ከሩብ ክፍለ ዘመን የስደት ህይወት በኋላ ወደ ሀገራቸው ሲመጡ በስፋት ያስተዋሉት ችግር በልብ ህክምና እጦት ምክንያት የሚሞቱ ህፃናትና ወጣቶች ቁጥር ማሻቀብ ነበር።
ያን ተከትሎ የችግሩን አሳሳቢነት የሚያሳይ አስፈላጊውን ጥናት በማድረግ ወደ ስዊድን ሃገር ተመልሰው የስዊድን መንግስትንና የስዊድን ፈንድ የመሳሰሉ አጋዥ ተቋማትን በማስተባበር ወደ ሀገራቸው ተመልሰው ለሀገሪቱ ብቸኛ የነበረውን የልብ ህክምና ሆስፒታል ያቋቁማሉ።
ሰኔ ዘጠኝ ቀን ሺ ዘጠኝ መቶ ዘጠና ዘጠኝ ዓ.ም አዲስ የልብ ህክምና ማዕከል ተመሠረተ።

የሃዘን መግለጫየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሕክምና ማኅበር በዶ/ር ፍቅሩ ማሩ ህልፈተ ሕይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ይገልፃል። ዶ/ር ፍቅሩ ፍፁም ሰብአዊነትን የተላበሰ በህክምናው ዘርፍ የ...
05/04/2025

የሃዘን መግለጫ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሕክምና ማኅበር
በዶ/ር ፍቅሩ ማሩ ህልፈተ ሕይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ይገልፃል።

ዶ/ር ፍቅሩ ፍፁም ሰብአዊነትን የተላበሰ በህክምናው ዘርፍ የፅናትን ዘር ዘርቶ፣ ብዙዎችን አፍርቶ የኖረ እንቁ ለአለማችን እና ለሀገራችን በልብ ህክምና ዘርፍ ተወዳዳሪ የሌለውን ስራዎች የሰራ እና በቀዳሚነት የተመደበ በሙያው ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል ያገለገለ ወንድም፣ ጓደኛ፣ አባት እና መካሪ ነበር።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሕክምና ማኅበር ውስጥም ከአባልነት እስከ የበላይ አማካሪነት እንዲሁም በለጋሽነት በማገልገል ሰብአዊነቱን በስራ ያስመሰከረ ለሁላችን ምሳሌ እና መኩሪያችን ነው።

የትንሳኤ ጌታ መድኃኒአለም ኢየሱስ ክርስቶስ የአባቴ ብሩካን ብሎ በቀኝ ካስቀመጣቸው ደጋግ አባቶቻችን ይደምርልን። ለቤተሰቡ እና ለሁላችንም መፅናናትን ያድልልን ።

In Loving Memory

Christ is Risen — the Savior of the world, who welcomed our beloved Dr. Fikru Maru to His right hand among the blessed.

Dr. Fikru was more than a healer — he was a quiet pioneer in the field of medicine, serving not for praise, but out of love, faith, and deep compassion. His strength, humility, and unwavering service touched many lives. He sowed seeds of healing, mentored with care, and built a legacy of kindness.

Though uncelebrated by the world, he was chosen by Christ — a faithful servant, devoted father, and friend to many.

His life’s journey is a guiding light for us all — a model of purpose, love, and service.

May our Lord Jesus Christ grant him eternal peace and provide comfort to all who grieve his loss.

Forever in our hearts.

Address

1511 Bankbury Way
Chesapeake, VA
23322

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Orthodox Tewahedo Medical Association posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Ethiopian Orthodox Tewahedo Medical Association:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram