Ethiopian Orthodox Tewahedo Medical Association

Ethiopian Orthodox Tewahedo Medical Association Nonprofit organization inspired by Faith, Hope and LOVE to provide a compassionate care for humanity

https://www.facebook.com/share/p/19wSEW4wnV/?mibextid=WC7FNe
05/04/2025

https://www.facebook.com/share/p/19wSEW4wnV/?mibextid=WC7FNe

አጭር የህይወት ታሪክ
(የቀጠለ.....)
ሆስፒታል ማቋቋም ብቻውን በዘርፉ ያለውን ችግር መቅረፍ እንደማይችል በማመን በርካታ የህክምና ባለ ሙያዎችን በራሳቸው /በዶ/ር ፍቅሩ/ ወጪ ስዊድን ድረስ በመላክ በልብ ህክምናው ስፔሻላይዝድ ያደረጉ እውቅ ሀኪሞችን በማፍራት የሰለጠነውን አለም የህክምና ሙያ ወደ ሀገር በማምጣት ለእውቀት ሽግግር ብርቱ ዋጋ ከፍለዋል። በዚህም በሰለጠነው አለም ብቻ ይሰጥ የነበረውን ውስብስብ የተባለ የልብ ህክምና ወደ ሀገራችን በማምጣት ጉልህ ሚና የተጫወቱ የሀገር ባለውለታ ናቸው, ካርዲዮሎጂስቱ ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ፡፡ ለወትሮው ህክምናውን ፍለጋ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ወደ ውጪ ይደረግ የነበረውን ጉዞ በማስቀረት ባለፉት ሁለት አስርት አመታት ሀገሪቱ ልታወጣ የምትችለውን የውጭ ምንዛሪ በማስቀረት አሻራቸውን ያኖሩት ዶ/ር ፍቅሩ፤ በአዲስ ካርዲያክ የማይሰጡ የልብ ህክምናዎች የሚደረግበትን ታዝማ የውስጥ ደዌ እና የቀዶ ልዩ ህክምና ማዕከልንም በመመስረትና አሁን ለደረሰበት ደረጃ
በማብቃት ዛሬ በርካታ ህፃናትና ወጣቶችን በልብ ህክምና እጦት ምክንያት ከሚነጥቀው ሞት መታደግ የቻሉ ታላቅ የሃገር ባለውለታ ናቸው።በጥቁር አንበሳ የሚሠጠውን የልብ ህክምና ለማዘመን ያላሰለሰ ጥረት ሲያደርጉ የቆዩት ዶ/ር ፍቅሩ በተለያዩ ጊዜያት በውድ ዋጋ የሚገዙ አላቂ የህክምና መሳሪያዎችን በእርዳታ በማቅረብ በርካታ አስተዋፆ አበርክተዋል።የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሲመሠረት በወቅቱ በነበሩት የጤና ሚኒስቴር ተመርጠው በተጣለባቸው ሃገራዊ ኃላፊነት መሠረት የግል የጤና ተቋማትን በማስተባበር ከመቶ ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ እንዲሰበሰብ በማድረግ ደማቅ አሻራቸውንም አኑረዋል። በጦርነቱ ወቅት የተጎዱ ት/ቤቶችንና ተቋማትን ለማገዝ በሚደረግ ርብርብ ውስጥ ሰፊ አበርክቶ የነበራቸውም ታላቅ ሰው ነበሩ።''በሀገርና በህዝብ ቂም የለም'' የዶ/ር ፍቅሩ ፅኑ እምነት ነው።ለሃገራቸው ፅኑ ፍቅር ያላቸው ዶ/ር ፍቅሩ ባለፈው ስርዓት በተለያየ ወቅት ለእስር ተዳርገዋል፡፡ ታድያ ስርዓተ ለውጡን ተከትሎ ከእስር ቤት ሲወጡ ዜግነት ወዳላቸው ስዊድን ሀገር ለህክምና ይጓዛሉ። በዛን ወቅት ተመልሰው አይመጡም ተብሎ ብዙ ሲናፈስ እርሳቸው ግን በጥቂት ሳምንታት ነበር ወደ ሀገራቸው ተመልሰው የገቡት። 'ይሄ ሁሉ በደል ደርሶብዎ እንዴት ወደ ሀገርዎ ሊመለሱ ቻሉ?' ተብለው ሲጠየቁ ምላሻቸው አጭርና ግልፅ ነበር '' በሀገርና በህዝብ ቂም የለም" ነበር ምላሻቸው።
ላለፉት አስራ ዘጠኝ አመታት በኪራይ ቤት አገልግሎት ሲሰጥ የቆየውን አዲስ የልብ ህክምና በዘርፉ የሀገሪቱ የልህቀት ማዕከል ለማድረግ ከነበራቸው ጥልቅ ፍላጎት በመነሳት ለመኖሪያነት በገዙት መሬት ላይ ደረጃውን የጠበቀ ባለ ስምንት ወለል ህንፃ በመገንባት በቅርቡ ሆስፒታሉን ወደ አዲስ ምዕራፍ በማሸጋገር ሂደት ላይ ነበሩ።
ነገር ግን ባጋጠማቸው የጤና እክል ምክንያት በስዊድን ሀገር ህክምናቸውን ሲከታተሉ ቆይተው በተወለዱ በ74 አመታቸው ከዚህ አለም ድካም አርፈዋል።
ካርዲዮሎጂስት ዶ/ር ፍቅሩ ባለትዳርና የሁለት ሴት ልጆች አባት እንዲሁም የአራት የልጅ ልጆች አያት ነበሩ።
የዶ/ር ፍቅሩ ማሩ የቀብር ስነ-ስርዓት በስዊድን ሀገር የሚፈፀም ሲሆን በሀገር ውስጥ ሀዘን መካፈል ለሚፈልጉ አዲስ አበባ ጃክሮስ እግዚአብሔር አብ ቤተ-ክርስቲያን አጠገብ - ከቪዥን ት/ቤት ጀርባ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው መድረስ የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
- ቤተሰቦቻቸው፣አዲስ የልብ ህክምና ሆስፒታል ማኔጅመንትና ሰራተኞች፤ታዝማ የውስጥ ደዌ እና የቀዶ ልዩ ህክምና ማዕከል ማኔጅመንትና ሰራተኞች ለቤተሰቦቻቸው እንዲሁም ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ

https://www.facebook.com/share/p/18uDWsMsbB/?mibextid=WC7FNe
05/04/2025

https://www.facebook.com/share/p/18uDWsMsbB/?mibextid=WC7FNe

አጭር የህይወት ታሪክ
በኢትዮጵያ በግል ህክምናው መስክ በሀገሪቱ የመጀመሪያ የሆነው የአዲስ የልብ ህክምና ሆስፒታል እና ታዝማ መስራች የሆኑት ካርዲዮሎጂስት ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ ከዚህ አለም ድካም ማረፋቸው ተገለፀ።
በአዲስ አበባ ፈረንሳይ ለጋሲዮን በተለምዶ ጉራራ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሺ ዘጠኝ መቶ አርባ ሶስት ዓ.ም የተወለዱት ካርዲዮሎጂስት ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ እድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ በኮከበ ፅባህ ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ት/ቤት የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል።
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውንም አሰላ በሚገኘው ራስ ዳርጌ ት/ቤት ተከታትለዋል።
በሺ ዘጠኝ መቶ ስልሳዎቹ መጀመሪያ ለሀገር ፍቅር ከነበራቸው ጥልቅ ስሜት በመነሳትም የኢትዮጵያ የአየር ኃይልነት ምልመላ ሲከናወን ትምህርታቸውን አቋርጠው የኢትዮጵያ አየር ኃይልን ተቀላቀሉ።
በወቅቱ አየር ኃይልን ለመቀላቀል ከተመለመሉ 27 እጩ አባላት መካከል በብቃት የአየር ኃይልነት ስልጠናን አጠናቀው በጀት አብራሪነት የተመረቁት 5 ብቻ ነበሩ፡፡ ከነዚህም ብቸኛው ጀት ስኳዶር ሆኖ የወጣው በዕድሜ ትንሹ የነበረው ፍቅሩ ማሩ ነበር።
በሺ ዘጠኝ መቶ ስልሳ ስድስት የአብዮቱን መፈንዳት ተከትሎ ደርግ ለስልጣኔ ስጋት ይሆናሉ ያላቸውን ግለሰቦች እያፈሰ ወደ እስር ቤት ማጋዝ ሲጀምር በሃገር ፍቅር ስሜት ተቆርቋሪነታቸው የሚታወቁትን የመቶ አለቃ ዶ/ር ፍቅሩንም ማሳደድ ይጀምራል፤ የህዝቦች እኩልነትና አንድነት ይረጋገጥ ዘንድ ይታገሉ የነበሩት ዶ/ር ፍቅሩም በደርግ እየታሰሱ መሆናቸውን ሲረዱ የሚወዱትን ሃገር ጥለው ወደ ሱዳን ይሰደዳሉ። ከዛም ወደ ስዊድን በመሻገር የስደት ህይወትን ይጀምራሉ።
በወቅቱ እሳቸውን መያዝ ያልቻለው ደርግም ሁለት ወንድሞቻቸውን ይገድልባቸዋል።
በስዊድን ቆይታቸው በሃገራቸው የዲሞክራሲ ስርዓት እንዲገነባ በመላው አውሮፓ የሚገኙ የኢህአፓ የተማሪዎች ንቅናቄን በመምራት ጉልህ ሚናን ከመጫወታቸው በላይ በልብ ህክምናው ዘርፍ ስፔሻላይዝ በማድረግ በእስካንዴኔቪያን ሃገራት ጭምር አንቱታን ያተረፉ ካርዲዮሎጂስት ናቸው።
በሺ ዘጠኝ መቶ ዘጠናዎቹ መጀመሪያ የኤች አይ ቪ ቫይረስ ስርጭት እንደሃገር ስጋት በደቀነ ግዜ የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት ሃገራዊ ጥሪ ሲደረግ በስዊድን ያሉ አጋር ድርጅቶችን በማስተባበር ወደ ሃገር ቤት ቀድመው ከዘለቁ የሀገር ባለውለታ መካከል አንዱ ናቸው, ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ
ከሩብ ክፍለ ዘመን የስደት ህይወት በኋላ ወደ ሀገራቸው ሲመጡ በስፋት ያስተዋሉት ችግር በልብ ህክምና እጦት ምክንያት የሚሞቱ ህፃናትና ወጣቶች ቁጥር ማሻቀብ ነበር።
ያን ተከትሎ የችግሩን አሳሳቢነት የሚያሳይ አስፈላጊውን ጥናት በማድረግ ወደ ስዊድን ሃገር ተመልሰው የስዊድን መንግስትንና የስዊድን ፈንድ የመሳሰሉ አጋዥ ተቋማትን በማስተባበር ወደ ሀገራቸው ተመልሰው ለሀገሪቱ ብቸኛ የነበረውን የልብ ህክምና ሆስፒታል ያቋቁማሉ።
ሰኔ ዘጠኝ ቀን ሺ ዘጠኝ መቶ ዘጠና ዘጠኝ ዓ.ም አዲስ የልብ ህክምና ማዕከል ተመሠረተ።

የሃዘን መግለጫየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሕክምና ማኅበር በዶ/ር ፍቅሩ ማሩ ህልፈተ ሕይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ይገልፃል። ዶ/ር ፍቅሩ ፍፁም ሰብአዊነትን የተላበሰ በህክምናው ዘርፍ የ...
05/04/2025

የሃዘን መግለጫ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሕክምና ማኅበር
በዶ/ር ፍቅሩ ማሩ ህልፈተ ሕይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ይገልፃል።

ዶ/ር ፍቅሩ ፍፁም ሰብአዊነትን የተላበሰ በህክምናው ዘርፍ የፅናትን ዘር ዘርቶ፣ ብዙዎችን አፍርቶ የኖረ እንቁ ለአለማችን እና ለሀገራችን በልብ ህክምና ዘርፍ ተወዳዳሪ የሌለውን ስራዎች የሰራ እና በቀዳሚነት የተመደበ በሙያው ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል ያገለገለ ወንድም፣ ጓደኛ፣ አባት እና መካሪ ነበር።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሕክምና ማኅበር ውስጥም ከአባልነት እስከ የበላይ አማካሪነት እንዲሁም በለጋሽነት በማገልገል ሰብአዊነቱን በስራ ያስመሰከረ ለሁላችን ምሳሌ እና መኩሪያችን ነው።

የትንሳኤ ጌታ መድኃኒአለም ኢየሱስ ክርስቶስ የአባቴ ብሩካን ብሎ በቀኝ ካስቀመጣቸው ደጋግ አባቶቻችን ይደምርልን። ለቤተሰቡ እና ለሁላችንም መፅናናትን ያድልልን ።

In Loving Memory

Christ is Risen — the Savior of the world, who welcomed our beloved Dr. Fikru Maru to His right hand among the blessed.

Dr. Fikru was more than a healer — he was a quiet pioneer in the field of medicine, serving not for praise, but out of love, faith, and deep compassion. His strength, humility, and unwavering service touched many lives. He sowed seeds of healing, mentored with care, and built a legacy of kindness.

Though uncelebrated by the world, he was chosen by Christ — a faithful servant, devoted father, and friend to many.

His life’s journey is a guiding light for us all — a model of purpose, love, and service.

May our Lord Jesus Christ grant him eternal peace and provide comfort to all who grieve his loss.

Forever in our hearts.

📣"ሕያውን ከሙታን ጋር ለምን ትሹታላችሁ? በዚህ የለም ፤ ተነስቷል። " ሉቃስ 24 : 5⛪️ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን - በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን፤⛪️አሰሮ ለሰይጣን - አግዐዞ ለአዳም፤⛪️ሰላም...
04/20/2025

📣"ሕያውን ከሙታን ጋር ለምን ትሹታላችሁ? በዚህ የለም ፤ ተነስቷል። " ሉቃስ 24 : 5

⛪️ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን - በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን፤
⛪️አሰሮ ለሰይጣን - አግዐዞ ለአዳም፤
⛪️ሰላም - እምይዕዜሰ፤
⛪️ኮነ - ፍስሐ ወሰላም
+ + +
⛪️ክርስቶስ በታላቅ ኃይልና ሥልጣን ከሙታን ተነሣ፤
⛪️ሰይጣንን አሰረው አዳምንም ነጻ አወጣው፤
⛪️ሰላም ከዛሬ ጀምሮ
⛪️ፍጹም ደስታና ሰላምና ሆነ!
⛪️እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው አደረሰን!!!
+ + +
⛪️Christ is risen from the dead! - By the highest power and authority!
⛪️He chained Satan! - Freed Adam!
⛪️Peace! Henceforth!
⛪️Is! Joy and Peace

Happy Resurrection Day!!!
April 20, 2025

"ሆሳዕናን ለህጻናት" ነጻ የሕክምና አገልግሎት ተሰጠ!የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር በየዓመቱ የሆሳዕና ዕለት የሚያከናውነውን እና "ሆሳዕናን ለህጻናት" የተሰኘውን ነጻ የሕክም...
04/14/2025

"ሆሳዕናን ለህጻናት" ነጻ የሕክምና አገልግሎት ተሰጠ!

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር በየዓመቱ የሆሳዕና ዕለት የሚያከናውነውን እና "ሆሳዕናን ለህጻናት" የተሰኘውን ነጻ የሕክምና አገልግሎት ለ2ኛ ጊዜ በተሳካ ሁኔታ ለመስጠት ቻለ።

የዘንድሮው አገልግሎት የተከናወነው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሴቶች ሕፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ስር በሚገኘው በክበበፀሐይ የሕፃናት ጊዜያዊ ማቆያና እንክብካቤ ማዕከል (Kibebetsehay Children Orphanage & Care Center) ውስጥ ለሚገኙ ህፃናት ሚያዝያ 5 ቀን ላይ ነበር።

በዕለቱም ዘርፈ ብዙ የሆነ የህክምና አገልግሎት የተሰጠ ሲሆን አጣዳፊ ሕክምና የሚያስፈልጋቸው 4 ህጻናት በመገኘታቸው ወደ የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ድንገተኛ ክፍል በሪፈራል ተልከዋል።

ለአገልግሎቱ መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላደረጉልን የማዕከሉ አመራሮችና ሰራተኞች የላቀ ምስጋና እናቀርባለ። በዚህም ነጻ የሕክምና አገልግሎት በበጎ ፈቃደኝነት የተሳተፉ ባለሙያዎች በተጠቃሚዎች ስም ከልብ እናመሰናለን።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር

“አክብሮትና ትህትናን የተላበሰ የጤና አገልግሎት ለሰው ልጆች በሙሉ”

2ኛው "ሆሳዕናን ለህጻናት" ነጻ የሕክምና አገልግሎት የቦታ ለውጥበናፍቆት የሚጠበቀው ልዩ ሕክምና ለሕፃናት ብቻ የሚሰጥበት "ሆሳዕናን ለህጻናት" የተሰኘው አገልግሎት ቀኑ እየደረሰ ነው። ይህ...
04/10/2025

2ኛው "ሆሳዕናን ለህጻናት" ነጻ የሕክምና አገልግሎት የቦታ ለውጥ

በናፍቆት የሚጠበቀው ልዩ ሕክምና ለሕፃናት ብቻ የሚሰጥበት "ሆሳዕናን ለህጻናት" የተሰኘው አገልግሎት ቀኑ እየደረሰ ነው። ይህ አገልግሎት የሚሰጠው በ ሆሳዕና ዕለት ሚያዝያ 5 ቀን (April 13) ላይ ሲሆን በዕለቱ በሙያችሁ በበጎ ፈቃደኝነት ለማገልገል የተመዘገባችሁ ባለሙያዎች በሙሉ የቦታ ለውጥ ማድረጋችንን ለማሳወቅ እንወዳለን።
አገልግሎቱ የሚሰጠው በክበበፀሐይ የሕፃናት ጊዜያዊ ማቆያና እንክብካቤ ማዕከል (Kibebetsehay Children Orphanage & Care Center) ስለሆነ በተጠቀሰው ቀን እና ሰዓት በቦታው እንዲገኙልን በአክብሮት እንጠይቃለን።

ቀን፡ ሚያዝያ 5 // Date: April 13
ሰዓት፡ ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ // Time: Starting from 9:00 AM
ቦታ፡ በክበበፀሐይ የሕፃናት ጊዜያዊ ማቆያና እንክብካቤ ማዕከል // Kibebetsehay Children Orphanage & Care Center።

ጥያቄ ካለዎት በ 0913789041 ይደውሉ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር

“አክብሮትና ትህትናን የተላበሰ የጤና አገልግሎት ለሰው ልጆች በሙሉ”

https://maps.app.goo.gl/aCZQFT3q2n7AjFEF7

2ኛው ሆሳዕናን ለህጻናት ነጻ የሕክምና አገልግሎት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር 2ኛውን "ሆሳዕናን ለህጻናት" የተሰኘውን ነጻ የሕክምና አገልግሎት ለህጻናት በስለ እናት በጎ ...
04/01/2025

2ኛው ሆሳዕናን ለህጻናት
ነጻ የሕክምና አገልግሎት

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር 2ኛውን "ሆሳዕናን ለህጻናት" የተሰኘውን ነጻ የሕክምና አገልግሎት ለህጻናት በስለ እናት በጎ አድራጎት ድርጅት ሚያዝያ 5 ቀን (April 13) ላይ ከተለያዩ የህጻናት የሕክምና ስፔሺያሊቲ በተውጣጡ ባለሙያዎች አገልግሎት ይሰጣል። በዚህ አገልግሎት ለመሳተፍ የምትፈልጉ ከዚህ በታች የተዘረዘሩ ባለሙያዎች የምዝገባ ቅጹን እስከ ሚያዝያ 3 ድረስ በመሙላት አውንታችሁን እንድታሳውቁን በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን።

ቀን፡ ሚያዝያ 5 // Date: April 13

ሰዓት፡ ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ // Time: Starting from 9:00 AM

ቦታ፡ በስለ እናት በጎ አድራጎት ድርጅት // Sele Enat Charitable Organization

ለዚህ አገልግሎት የሚያስፈልጉ ባለሙያዎች የሚከተሉት ናቸው፦

Specialties needed are:

Pediatricians
Pediatric Neurologist
Pediatric Surgeon
Pediatric Orthopedic Surgeon
Dermatologists
General Practitioner
Nurses
Speech Therapist
Physiotherapist

የጤና ባለሙያዎች ለመመዝገብ ቅጹን ይሙሉ። ምዝገባ የሚያበቃበት ቀን ሚያዝያ 3 ነው።
https://forms.gle/Lhg28uFsaatsecCg7

ጥያቄ ካለዎት በ 0913789041 ይደውሉ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር

“አክብሮትና ትህትናን የተላበሰ የጤና አገልግሎት ለሰው ልጆች በሙሉ”

03/30/2025

3ኛው ዓመታዊው "መጻጉዕን በመቄዶንያ" ነጻ የሕክምና አገልግሎት Part 1

ከ 5 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የሕክምና አገልግሎት ተሰጠ3ኛው ዓመታዊው "መጻጉዕን በመቄዶንያ" ነጻ የሕክምና አገልግሎት ተጠናቀቀ።የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር በየዓመቱ ...
03/24/2025

ከ 5 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የሕክምና አገልግሎት ተሰጠ

3ኛው ዓመታዊው "መጻጉዕን በመቄዶንያ" ነጻ የሕክምና አገልግሎት ተጠናቀቀ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር በየዓመቱ የሚያደርገውን "መጻጉዕን በመቄዶንያ" ነጻ የሕክምና አገልግሎት ከመጋቢት 7 እስከ መጋቢት 14 ለተከታታይ 8 ቀናት ሲያካሂድ ቆይቶ በተሳካ ሁኔታ ለማጠናቀቅ ቻለ።

በዚህ አገልግሎት ዘርፈ ብዙ የሕክምና አገልግሎት ከተሟላ ላቦራቶሪ እና ዲያግኖስቲክ ምርመራ ጋር ለመስጠት ተችሏል።

ከአዲስ የልብ ሕክምና ሆስፒታል (Addis Cardiac Hospital) ጋር በመተባበር በልብ ሐኪሞች የተሟላ የልብ ሕክምና የተሰጠ ሲሆን ለ 17 ታካሚዎች የልብ አልትራሳውንድ (Echocardiography) እና ለ 12 ታካሚዎች የ ኢሲጂ (ECG) ምርመራ ተሰርቶላቸዋል።

ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የዓይን ሕክምና ክፍል ጋርም በመተባበር የተሟላ የዓይን ሕክምና የተሰጠ ሲሆን 80 በዓይን ሞራ ግርዶሽ (Cataract) ተጠቂ የሆኑ ታካሚዎች ተለይተው በዳግማዊ ምኒልክ ሆስፒታል የቀዶ ሕክምና አገልግሎት ለመስጠት ተመቻችቷል።

በአንጀት እና ጉበት ስፔሺያሊስት ሐኪሞች ለ 6 ታካሚዎች የኢንዶስኮፒ (Endoscopy) መርመራ ተደርጓል።

በአጥንት ሐኪሞች የተለያዩ ፕሮሲጀሮች የተሰሩ ሲሆን የፊዚዮቴራፒ ሕክምናም ተሰጥቷል።

በጥርስ ሕክምና ከፍልም የተሟላ የጥርስ ሕክምና በመስጠት ለ 20 ታካሚዎች የጥርስ ነቀላ (Dental extraction) ለማድረግ ተችሏል።

በ ኢንተርናሽናል ክሊኒካል ላቦራቶሪ ለ 1000 ታካሚዎች የተሟላ የላቦራቶሪ ምርመራ እና በ አርሾ ሜዲካል ላቦራቶሪ ደግሞ ለ 150 ታካሚዎች የስኳር በሽታ (HbA1c) ምርመራ ተሰጥቷል። 115 ታካሚዎችም የአልትራሳውንድ ምርመራ ተደርጎላቸዋል።

በዚህ አገልግሎት 241 ከተለያዩ የሕክምና ስፔሺያሊቲ እና የጤና ሙያ የተውጣጡ ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ 9 ሰብስፔሺያሊስት ሐኪሞች ፣ 50 ስፔሺያሊስት፣ 105 ጠቅላላ ሐኪሞች፣ 42 ነርሶች፣ የጥርስ ሐኪሞች፣ ፋርማሲስቶች፣ ፊዚዮቴራፒስቶች፣ የስነእምሮ እና የማኀበረሰብ ጤና ባለሙያዎች እንዲሁም የላቦራቶሪ ቴክኒሺያኖች ይገኙበታል።

1,646 ታካሚዎች በዚህ አገልግሎት የተለያዩ የሕክምና አገልግሎቶች ተጠቃሚ የሆኑ ሲሆን አጠቃላይ የተሰጠው የሕክምና አገልግሎትም በገንዘብ 5,416, 850 ብር የሚገመት ነበር።

ለዚህ አገልግሎት መሳካት የረዳችሁንን አዲስ የልብ ህክምና ሆስፒታል (ADDIS CARDIAC HOSPITAL) ፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ
የዓይን ሕክምና ክፍል ፣ አርሾ ሜዲካል ላቦራቶሪ (Arsho medical labratories P.L.C) ፣ ኢንተርናሽናል ክሊኒካል ላቦራቶሪ (International clinical laboratories) ፣ አበበች ጎበና የእናቶች እና ህፃናት ሆስፒታል (Abebch Gobena MCH Hospital) ፣ ያኔት አጠቃላይ ሆስፒታል (YANET GENERAL HOSPITAL) ፣ BADREG PHARMACEUTICALS, ELPIS PHARMACEUTICALS, HAKIM PAGE
DR. DEBOL, MEDICAL INFORMATION በአገልግሎቱ ተጠቃሚ በሆኑት ወገኖቻችን ስም ለማመስገን እንወዳለን።

በዚህ አገልግሎት ለጤና ባለሙያዎች የምግብ አቅርቦት ድጋፍ ላደርጉልን ሼፍ ቤኪ ኬቴሪንግ እና ሬስቶራንትም (Shef Beki Catering & Restaurant) የላቀ ምስጋና እናቀርባለን።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር

“አክብሮትና ትህትናን የተላበሰ የጤና አገልግሎት ለሰው ልጆች በሙሉ”

03/22/2025

3ኛው "መጻጉዕን በመቄዶንያ" ነጻ የሕክምና አገልግሎት የመዝጊያ መርሐግብር
መጋቢት 14 / March 23 ከጠዋቱ 3፡30 / 9:30 AM ጀምሮ በመቄዶንያ የአረጋውያንና አእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል ይካሔዳል።
የጤና ባለሙያዎች ብቻ ሳይሆን ሁላችሁም በመዝጊያው መርሐግብር እንድትገኙ ተጋብዛችኋል!
የሚዲያ ባለሙያዎችም በቦታው በመገኘት ይህን ታላቅ አገልግሎት ትዘግቡ ዘንድ ተጋብዛችኋል!

03/22/2025

"መጻጉዕን በመቄዶንያ" ነጻ የሕክምና አገልግሎት እንደቀጠለ ነው።

አገልግሎቱ የሚያበቃው እሑድ ሲሆን ለ ቅዳሜ እና ለ እሑድ ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ባለሙያዎች በተጨማሪ ያስፈልጋሉ። የተመዘገባችሁ የጤና ባለሙያዎች በሰዓቱ እንድትገኙልን ከታላቅ አክብሮት ጋር ለማሳሰብ እንወዳለን።
በተጨማሪ የሚያስፈልጉ Specialist/subspecialists:
Neurologist
Psychiatrist
Neuropsychiatrist
Dermatologist
Internist
Cardiologist
ENT specialists
Endocrinologist
Nutritionist
Rheumatologist
Orthopedics

ጥያቄ ካለዎት በ 0913789041 ይደውሉ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር
“አክብሮትና ትህትናን የተላበሰ የጤና አገልግሎት ለሰው ልጆች በሙሉ”

"መጻጉዕን በመቄዶንያ" 3ኛ ቀን መጋቢት 9 / March 18ደስ የሚል አገልግሎት ነበር። በዚህ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ የተሳተፋችሁ የጤና ባለሙያዎች በሙሉ በተጠቃሚዎቹ ስም የላቀ ምስጋ...
03/19/2025

"መጻጉዕን በመቄዶንያ" 3ኛ ቀን
መጋቢት 9 / March 18

ደስ የሚል አገልግሎት ነበር።
በዚህ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ የተሳተፋችሁ የጤና ባለሙያዎች በሙሉ በተጠቃሚዎቹ ስም የላቀ ምስጋና እናቀርባለን።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር

“አክብሮትና ትህትናን የተላበሰ የጤና አገልግሎት ለሰው ልጆች በሙሉ”

Address

1511 Bankbury Way
Chesapeake, VA
23322

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Orthodox Tewahedo Medical Association posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Ethiopian Orthodox Tewahedo Medical Association:

Share